የመለከት ድምፅ መጽሔት ቁጥር 5 ዛሬ ወጥቶአል

የመለከት ድምፅ መጽሔት ቁጥር 5 ዛሬ ወጥቶአል። በዚህ እትም ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረው በመጨረሻው ቀን በተለይም የሃሰተኛውን ክርስቶስን መምጣት ተመልክቶ ብዙዎችን ወደ ስህተት ሊያስገቡ የሚችሉ ሃሳቦችን፣ ፍልስፍናዎችን እና የተሳሳቱ ሃይማኖታዊ እምነቶችን ዋነኛ መሰረቶች በተመለከተ አጠር ያለ ጽሁፍ ቀርቦአል። በተጨማሪም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽፋን እየተዘጋጀ ስላለው ስለኔፊሊምና የሃሰተኛው ክርስቶስ መምጣት ስውር ዝግጅቶች፣ በነዚህ ወራት እጅግ እየበዛ ስለመጣው አለም አቀፋዊ ጦርነቶች ዝግጅትና የጦርነት ወሬ፣ በዱባይ ስለተካሄደው አምስተኛው የዓለም መንግስት ጉባኤ ዘገባ፣ አጠር አጠር ያሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንተናዎች ቀርበዋል። በመጨረሻም በመከራና በፈተና የምናልፍ ክርስቲያኖች ሁሉ እውነተኛና ዘላቂ መጽናናትን የምናገኘው እንዴትና ከየት ነው በሚለው ጥያቄ ላይ አጠር ያለ ትምህርት ቀርቧል። በPDF የተዘጋጀውን የመጽሄቱ ኤሌክትሮኒክ ቅጂ ከላይ ተሰጠው ማግኘት ይቻላል። በጊዜ እጥረት በየወሩ ይቀርብ የነበረው ምስክርነት ቁጥር 4 በዚህ እትም አልደረሰም። በሚቀጥለው ቁጥር 6 ላይ እንደሚቀርብ የምናስታውቀው ከይቅርታ ጋር ነው። ጥያቄና አስተያየታችሁን ብትልኩልን ደስ ይለናል። ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ ብርሃኑ አድማሱ

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...