የመለከት ድምፅ መጽሔት ቁጥር 5 ዛሬ ወጥቶአል። በዚህ እትም ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረው በመጨረሻው ቀን በተለይም የሃሰተኛውን ክርስቶስን መምጣት ተመልክቶ ብዙዎችን ወደ ስህተት ሊያስገቡ የሚችሉ ሃሳቦችን፣ ፍልስፍናዎችን እና የተሳሳቱ ሃይማኖታዊ እምነቶችን ዋነኛ መሰረቶች በተመለከተ አጠር ያለ ጽሁፍ ቀርቦአል። በተጨማሪም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽፋን እየተዘጋጀ ስላለው ስለኔፊሊምና የሃሰተኛው ክርስቶስ መምጣት ስውር ዝግጅቶች፣ በነዚህ ወራት እጅግ እየበዛ ስለመጣው አለም አቀፋዊ ጦርነቶች ዝግጅትና የጦርነት ወሬ፣ በዱባይ ስለተካሄደው አምስተኛው የዓለም መንግስት ጉባኤ ዘገባ፣ አጠር አጠር ያሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንተናዎች ቀርበዋል። በመጨረሻም በመከራና በፈተና የምናልፍ ክርስቲያኖች ሁሉ እውነተኛና ዘላቂ መጽናናትን የምናገኘው እንዴትና ከየት ነው በሚለው ጥያቄ ላይ አጠር ያለ ትምህርት ቀርቧል። በPDF የተዘጋጀውን የመጽሄቱ ኤሌክትሮኒክ ቅጂ ከላይ በተሰጠው ማግኘት ይቻላል። በጊዜ እጥረት በየወሩ ይቀርብ የነበረው ምስክርነት ቁጥር 4 በዚህ እትም አልደረሰም። በሚቀጥለው ቁጥር 6 ላይ እንደሚቀርብ የምናስታውቀው ከይቅርታ ጋር ነው። ጥያቄና አስተያየታችሁን ብትልኩልን ደስ ይለናል። ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ ብርሃኑ አድማሱ
የመለከት ድምጽ ብሎግ የአማርኛን ቋንቋ በተቀዳሚነት ለሚጠቀሙ ሰዎች በሙሉ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የወንጌል የምስራች ለማድረስ፣ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላመኑ ክርስቲያኖች ደግሞ መሰረታዊ የሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችን ለማስተማር ያገለግላል።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
አስተያየቶች ለጥፍ (Atom)
ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ
በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...
-
የኖኀ ዘመን ፥ ኔፊሊም እነማን ናቸው? ከየት መጡ? ምን አደረጉ? ፍጻሜያቸውስ? ትምሕርት 5 ዘፍጥረት ምዕራፍ 6 “በዚያን ወራት ኔፊሊም በምድር ላይ ነበሩ ደግሞም ከዚያ በኋላ የእግዚአብሔር ልጆች የሰውን ሴቶች ...
-
የኖህ ዘመን እንደነበር የጌታ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል፡ ኔፊሊም ከየት መጡ? ከሰው ሴቶች ልጆች የወለዷቸው እነዚያ “የእግዚአብሔር ልጆች” የተባሉት እነማን ናቸው? ትምሕርት 6 ባለፉት 5 ትምህርቶች ጌታ ኢየሱስ...
-
ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፣ እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ። ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብጹዓን ...
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ