የእንግሊዝ መንግስት መጽሐፍ ቅዱስ እንደገና መተርጎም አለበት፣ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርት ቤቶችና የእሁድ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርቶችም ሳይቀሩ ሰዶማዊነት ትክክል መሆኑን ማስተማር አለባቸው የሚል ሪፖርት አወጣ።

የእንግሊዝ መንግስት መጽሐፍ ቅዱስ እንደገና መተርጎም አለበት፣ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርት ቤቶችና የእሁድ የመጽሃፍ ቅዱስ ትምህርቶችም ሳይቀሩ ሰዶማዊነት ትክክል መሆኑን ማስተማር አለባቸው የሚል ሪፖርት አወጣ። ዜናውን ከዚህ ማገናኛ ማግኘት ይቻላል። http://www.wnd.com/2017/07/u-k-govt-demands-queer-theology-in-seminaries/
ዊልተን ፓርክ የሚባለው የእንግሊዝ መንግስት  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ የመጽሐፍ ቅዱስ ማስተማሪያ ኮሌጆች፣ ዩኒቨርሲቲዎችና ሴሚናሪዎች ሰዶማዊነትን የሚያስረዱና የሚደግፉ ትምህርቶችን እንዲያዘጋጁ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ራሱም እንደገና እንዲተረጎምና ሰዶማዊነትን የሚቃወሙ ክፍሎች ውስጥ ያሉት ሃሳቦች መከለስ አለባቸው የሚል ሪፖርት አወጣ። በምእራብ አውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካና በሌሎችም ሰለጠኑ በሚባሉ አገሮች ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ከመዳከማቸው የተነሳ ሰዶማዊነትን ወይም ሌሎች ኢመጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆኑ የአኗኗር ዘይቤዎችን ስለማይቃወሙ፣ የሪፖርቱ ትኩረት የክርስትና እምነት ጠንካራ በሆነባቸው በአፍሪካ፣ በደቡብ አሜሪካና ሌሎችም መጽሃፍ ቅዱሳዊ እምነት ጠንካራ በሆነባቸው አገሮች ላይ ነው።  ወገኖች፣ በትንቢተ ዳንኤል ምእራፍ 7 ቁጥር 25 ላይ ሃሰተኛው ክርስቶስ ጌታ አምላክ የደነገጋቸውን ህግጋትንና ዘመናትን ይለውጣል ተብሎ የተጻፈው መፈጸም ከጀመረ ውሎ አድሮአል። ምናልባት የጌታ መምጣት በጣም ሩቅ የሚመስለን ካለን ከእንቅልፍ የምንነሳበት ጊዜ እንዳያልፍብን ቶሎ እንንቃ። ከላይ የተጠቀሰውን ሪፖርት ለማንበብ የሚፈልግ ሰው ሪፖርቱን ከሚከተለው ድረ ገጽ ማገናኛ (link) ማግኘት ይችላል። https://www.wiltonpark.org.uk/wp-content/uploads/WP1488-Report.pdf


ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...