የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ስልጣን በመጋፋት አየሩን ለመለወጥ እየጣረ ነው

የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ስልጣን በመጋፋት አየሩን ለመለወጥ እየጣረ ነው
ታላላቆቹና ባለጸጎቹ አገሮች የምድርን አየር እንደፈለጉት በመለዋወጥ ሲያሻቸው ዝናብ፣ ሲፈልጉ ማእበል፣ ሳይፈልጉ ደግሞ ድርቅ የሚያስነሱበት ቴክኖሎጂ አላቸው የሚለው ዜና አዲስ አይደለም። የአሜሪካ መንግስት ምክር ቤት በሰፊው ተወያይቶበት ችላ ብሎ የተወው ነገር ነው። ይሁን እንጂ ብዙ ሰው አሁንም ይህ መረጃ የለውም ብዙው ደግሞ እውነት ነው ብሎ ለመቀበል አይፈልግም። ሰው የእግዚአብሔርን ስልጣን በዚህና በሌሎች መስመሮችም መጋፋት ከጀመረ ውሎ ቢያድርም የዚህ ዓይነቱ ስራ የመጨረሻ ውጤቱ ጥፋት ነው።  ስለ ቴክኖሎጂውና ስለ ሰው ድፍረት ጥርጥሩ አሁንም ላለን ሰዎች የተያያዘው ዜና ይህ በምእራቡ ዓለም የተጀመረው አየርን የመለወጥና ሰው ሰራሽ ዝናብ የማዝነብ ስራ ዛሬ ደግሞ ወደ በቻይና እንደ ተስፋፋ ያመለክታል። አስተያየት ከመስጠት በፊት የተያያዘውን ዜና በጥሞና አንብቡት።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...