የመለከት ድምጽ ድረ ገጽ በከፊል በስራ ላይ ዋለ

የመለከት ድምጽ ድረ ገጽ በከፊል በስራ ላይ ዋለውድ ወገኖቼ፣ ምናልባት እንደ ሰማችሁት እንደዚህ እንደ ፌስቡክ ያሉ ማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች እስካሁን በነጻ የሚሰጡት አገልግሎት በዚሁ መንገድ ላይቀጥል ይችላል። ስለዚህም የመለከት ድምጽ አገልግሎትም የራሱ የሆነ ድረ ገጽ ስላስፈለገው ባለፉት ብዙ ወራት ሲታቀድና ሲገነባ ከቆየ በኋላ አሁን በከፊል በስራ ላይ ውሏል። ይህ ድረ ገጽ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ዳግም ምጽዓት የሚመለከቱ መልእክቶች፣ ዜናዎችና ትንተናዎችን፣ ትምህርታዊ ጽሁፎች፣ መንፈሳዊ መዝሙሮችና ቪዲዮ የሚቀርቡበት ይሆናል። ድረ ገጹ አሁንም በግንባታ ላይ ስላለ ከላይ ከተጠቀሱት አንዳንዶቹ ይዘቶች ገና በስራ ላይ አልዋሉም። ባለፈው አንድ ዓመት ተኩል የቀረቡ ጽሁፎችን፣ የመለከት ድምጽ መጽሔት ያለፉ እትሞችን እና ትንቢት ነክ ዜናዎችን በድረ ገጹ ላይ አቅርበናል። እንዲሁም ከዚህ በፊት በገበያ ላይ ያልዋሉ ከ20 የሚበልጡ በዚህ አገልግሎት ፕሬዝደንት የተደረሱና የተዘጋጁ መዝሙሮችን በማዳመጥ ጌታን እንድታመልኩት፣ እንድትጽናኑና እንድትበረታቱ ተጋብዛችኋል። አስተያየቶችን እና ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ዝግጅታችን ስላልተጠናቀቀ ለጊዜው እንድትታገሱን እንጠይቃለን። የድረ ገጹ አድራሻ: http://www.voiceoftrumpet.org (የመለከት ድምጽ አገልግሎት) ነው።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...