የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ሰዎች ሁሉ ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት እንዲዘጋጁ አሳሰቡ።

የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ሰዎች ሁሉ ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት እንዲዘጋጁ አሳሰቡ።
የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ የምስራቹ ወንጌል ከመንግሥታት ቁንጮዎች እስከ ተራው ሰው ድረስ በአንድም በሌላም መንገድ እየደረሰ ነው። በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው የዘለዓለም ሕይወትን ገና ያላገኙትን ሁሉ በፍቅር ወንጌሉ ለመጋበዝና፣ በእርሱ ያመኑት ሁሉ ደግሞ የዳግም ምጽዓቱ ተስፋ መቃረቡን በማወቅና በማመን እንዲበረታቱ እግዚአብሔር ትንንሾችንም ትልልቆችንም ሰዎች እየተጠቀመ ነው። በአገራቸው በናይጄሪያ የፕሬዝደንትነት አገልግሎት ጊዜአቸውን ሲጨርሱ የመንግስትን ሥልጣንን በሰላም ለሚቀጥለው መሪ በማስረከባቸው እንደ መልካም መሪ ምሳሌ ከሚጠቀሱት የአፍሪካ መሪዎች አንዱ የሆኑት የቀድሞው ጀነራል ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ የምድር ነገስታት ሁሉ ንጉስ፣ የጌቶቹም ሁሉ ጌታ የሆነው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት መድረሱን መናገራቸው ብዙ ሰባኪዎች አስተማሪዎች የሚናገሩት ቢሆንም፣ በህዝቧ ብዛት በአፍሪካ አንደኛ የሆነችው የዚህ አገር ፕሬዝደንት የነበሩት እኒህ ሰው ይህን እውነት በአደባባይ መናገራቸው ለብዙ ሰዎች ምስክርነት ነው።

እስከ ጥቂት አሰርት ዓመታት ድረስ የክርስትና እምነት ዋና ምሰሶዎች ነን ሲሉ የነበሩት የምእራቡ ዓለም አብያተ ክርስቲያንና መንግስታት የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት ጥለውና ወንጌልን ረስተው ወደ ባዕድ አምልኮ እየገቡ ባለበትና ሰለጠነ የሚባለው ዓለም ብዙ ህዝብ ፈሪሃ እግዚአብሔርንና ሰብዓዊ ህሊናን ጥሎ ለሰዶምና ለገሞራ እንኳን ያልበጀ የዓመጽ የኑሮ ዘይቤን እንደ ጌጥ እያንጠለጠለ ያዙኝ ልቀቁኝ በሚልበት በዚህ ዘመን፣ እግዚአብሔር ድሃና ያልተማረ ተብሎ በባለጸጋው ዓለም ወደታች ይታይ ከነበረው ከአፍሪካ የወንጌልን እውነት ለዓለም ሁሉ ሲልክ ማየቱ እጅግ አስደናቂ የፈጣሪ ስራ ነው። በእርግጥም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ተመልሶ ይመጣል። ቀኑንና ሰዓቱን አናውቅም፣ ለማንኛውም ግን ማንም ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ እግዚአብሔር መድረስ አይችልምና ንስሃ ገብቶ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የመቀበያው ሰዓት ዛሬ ነው። ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...