የሰውን ልጅ ጭንቅላትና ሰውነት ከኮምፒውተር ቴክኖሎጂ ጋር በቀጥታ በማያያዝ የማሻሻል ስራ እየተጧጧፈ ነው።

http://endtimeheadlines.org/2017/04/upgraded-humans-will-become-next-billion-dollar-industry/

እግዚአብሔር የፈጠረው በቂ አይደለም፣ እርጅናንና ሞትንም እናጠፋለን የሚሉ "ደካማ" የሆነውን የሰውን ጭንቅላትና ሰውነት የማሻሻሉ ስራ መጀመሩን የሚያበስሩ ዜናዎች በተደጋጋሚ እየወጡ ነው። ይህ የተያያዘውም ከነዚሁ ዜናዎች አንዱ ነው። ምናልባት ይህ ቀልድ ወይም ብቅ ብሎ የሚጠፋ የሚመስለው ካለ፣ ታላላቆቹ የምድር ኩባንያዎች ብዙ ቢሊዮን ብር በማፍሰስ ላይ እንዳሉና ከነዚህም ቴክኖሎጂዎች የመጀመሪያዎቹ እየተሰሩና እየተፈተሹ መሆኑን ልብ ይበል። ከዚህ ዜና ጋር ተያይዞ የቀረበው HOMO DEUS የተባለውና አዲስ የወጣ መጽሐፍ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ መረጃና እውቀት ለሚፈልጉ መልካም ንባብ ነው። የሆህን ዘመን በሚመስል ዘመን እየኖርን እንዳለ እናስተውል። በኖህ ዘመን የሰው ትእቢትና ኃጢዓት ሰማይ ስለደረሰ ነበር የዚያን ጊዜው ዓለም በውኃ የጠፋው። ገንዘብ ያለው የተሻሻለ ሰው እንዲሆን ቴክኖሎጂ ሲገጠምለት፣ ብ የሌለውን ደግሞ ምን ያደርጉት ይሆን።  የፈለጉት ሁሉ ይሳካለቸዋል ማለት አይደለም። ሊፈጥሩት የሚችሉት ጥፋት ግን በቀላሉ ሊገመት አይገባም። ዚህ የምድር ባለጸጎችና አዋቂ ነን ባዮች እንደሚያስቡት ሰው በአጋጣሚ ወደዚህ ዓለም ብቅ ያለ ቁስ ሳይሆን፣ በሚወደው አምላኩ በብዙ ጥንቃቄ ውብና ድንቅ ሆኖ የተሰራ ፍጥረት ነው። ዲያብሎስ በመጀመሪያ አዳምንና ሄዋንን በማታለል ከአምላካቸው ለይቶ በኃጢዓት እንዲወድቁና ወደ ሞት እንዲገቡ ገፋፋቸው። ዛሬ ደግሞ እርጅናን ታጠፋላችሁ፣ እንደ አምላክ የሚሆን እውቀትና ችሎታ ይኖራችኋል በሚል መልኩን ቀየር አድርጎ በመጣ ስህተት ይህችንም በጌታ ምህረት የቀረችለትን የምድር ሰባና ሰማንያ ዓመት እድሜው ለማፈራረስ ጠላት ቆርጦ ተነስቷል። የገዛናቸው ኮምፒውተሮች አስር ጊዜ መብራት መጥፋታቸው፣  አንዴ ቫይረስ ያዘው፣ አንዴ HACK ተደረገ፣ አንድ ጊዜ upgrade አድርጉ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ network የለም፣ እየተባልን ቁም ስቅል ማየቱ ቀረና ጭራሹኑ ብለው ብለው ፈጣሪ የሰጠንን ሰውነት ከምናምን ጋር ሊቀጣጥሉት መከጀላቸው ምን ያህል የሰው ትእቢት ከፍ እንዳለ የሚያመለክት ብቻ ሳይሆን፣ የሰው ልጅ የሚሄድበትን አቅጣጫ ምን ያህል እንደሳተም የሚያስረዳ ነው። ልብ ያለው ልብ ይበለው። በመለከት ድምጽ ቁጥር 6 ላይ እንዳቀረብኩት፣ ኮቤ ጃፓን በሚገኘው የRIKEN RESEARCH INSTITUTE ባደረገው ጥናት እንደተመለከተው የሰው ጭንቅላት በአንድ ሰከንድ ውስጥ የሚሰራቸውን ስራዎች ለመስራት 82,944 የኮምፒውተር ጭንቅላቶች (processors) በአንድ ላይ ተያይዘው ለመስራት የፈጀባቸው ጊዜ 40 ደቂቃ ነበር። ለአንድ ሰከንድ የሰው ጭንቅላት ስራ ይህ ሁሉ ኮምፒውተር ከተሰለፈ፣ ራሳችን በቀን የሚያከናውነው ለማድረግማ ምን ያህል ኮምፒውተሮች ይሰለፉ ይሆን። የሰውን ጭንቅላት፣ ችሎታና የእድሜ ገደብ እናሻሽላለን በሚል ሰበብ ሊያደርጉ ያቀዱት ምን ይሆን ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። ምንም ያድርጉ ምን፣ ለሰው ልጅ ከስጋዊም ሆነ ከዘለዓለማዊው ሞት የመዳኛ መንገድ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። እድሜን የሚሰጥ የሚያሳጥርም እግዚአብሔር ብቻ ነው። እግዚአብሔር የፈጠረው ይህ ሰውነታችን ግሩምና ድንቅ ነው። ነገር ግን፣ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ሊሆን ያለው ሁሉ ይሆናል። እግዚአብሔር መልካም ነው። ቅኖችንና እርሱን የሚሹትን ሁሉ ለክፉ አሳልፎ አይሰጥም። ስለዚህ በእርሱ የሚያምን ሁሉ መታወክ የለበትም። ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለው ህይወት አለው። በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላላመኑ ሁሉ ደግሞ የጌታ አምላክ የፍቅር እጆች አሁንም እንደተዘረጉ ናቸው። ያለ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሌላ የዘለዓለም ህይወት መንገድም ዋስትናም የለም። ስለዚህ ቀኑ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ ወደ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመምጣት ከዚህ ቀውጢ ዘመን እናምልጥ። ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ።


ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...