ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ኃያላኑና ባለጸጎቹ አገሮች ወይም ድርጅቶች የምድርን አየር ንብረት እንዳሻቸው ለመለወጥ መቻላቸው ይፋ እየሆነ ነው።

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ኃያላኑና ባለጸጎቹ አገሮች ወይም ድርጅቶች የምድርን አየር ንብረት እንዳሻቸው ለመለወጥ መቻላቸው ይፋ እየሆነ ነው። http://www.newsweek.com/artificially-cool-earth-volcano-eruptions-extremely-dangerous-711203
ከብዙ ሳምንታት በፊት በላክሁት መልእክት ሃብታሞቹ አገሮች ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በሚፈልጉት ቦታና ጊዜ ደመና እንዲፈጠር፣ ዝናብ እንዲዘንብ ወይም እንዳይዘንብ፣ ነጎድጓድና መብረቅ እንዲሁም በምእራቡ ዓለም ሃሪኬን (Hurricane) በእስያ ደግሞ ታይፉን (Typhoon) የሚባሉ ከፍተኛ ጥፋት የሚያደርሱ የአየር ማእበሎችን መፍጠር እንደሚችሉ ተጠቁሞ ነበር። ለብዙ አሰርት ዓመታት የዚህ ቴክኖሎጂ መኖርና በቬትናምና ሌሎችም ቦታዎች ላይ አሜሪካ ይህን ቴክኖሎጂ ለጦርነት ማዋሏ ሲካድ ከቆየ በኋላ ጉዳዩ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በአሜሪካ ምክር ቤትም ሳይቀር ውይይት የሚካሄድበት ሆኗል። ይህን ማገናኛ (link) በመጠቀም የአሜሪካው ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ ያደረገውን ስብሰባ የተመለከተ ዜናን ማግኘት ይቻላል፡http://www.homelandsecuritynewswire.com/us-congress-holds-hearings-geoengineering
ከዚህ መልእክት ጋር በተያያዘው ዜና እንደምታነቡት የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ የሚለቅቀውን አቧራ ዓይነት ሰው ሰራሽ ግርዶሽ በምድር ከባቢ አየር ላይ በመፍጠር የምድርን ከባቢ አየር የሚያሞቀውን የጸሃይ ብርሃን በመቀነስ በሰሜን ዋልታ አካባቢ በተፈለገው ጊዜ ቀዝቃዛ አየር በመፍጠር አሜሪካን በየጊዜው የሚጎዷትን ታላላቅ የአየር ማእበሎች (hurricanes) ለመቀነስ እንደሚቻል ቴክኖሎጂውን በቅርብ የሚያውቁ ባለሙያዎች ስለ ጉዳዩ ያላቸውን ፍራቻ በአደባባይ መዘገብ ጀምረዋል። በእንግሊዝ የሚገኘው የኤግዘተር ዩኒቨርሲቲ ዋነኛ ተመራማሪ የሆኑት አንቶኒ ጆንስ የተባሉት ባለሙያ Nature Communications በሚባለው መጽሔት ላይ እንዳሰፈሩት ይህ ቴክኖሎጂ በሰሜናዊው የምድር ግማሽ ስራ ላይ ሲውል በአሜሪካና በካሪቢያን አገሮች አካባቢ የሚከሰቱትንና ብዙ ጥፋት የሚያደርሱትን የአየር ማእበሎች ሲቀንስ፣ በሌላ ወገን ደግሞ በአፍሪካ የሳሄል አካባቢ ከፍተኛ ድርቅን ያስከትላል። ቴክኖሎጂው በደቡባዊው ክፍለ ዓለም በስራ ላይ ቢውል ደግሞ አሜሪካንና የካሪቢያን አገሮችን በየጊዜው የሚጎዱትን የአየር ማእበሎች እንደሚያባብስም ተደርሶበታል ይላል ይኸው ከላይ የተጠቀሰው ሪፖርት። በመቀጠልም ሪፖርቱ ገንዘቡና ቴክኖሎጂው ያላቸው አገሮች ወይም ድርጅቶች ይህን ቴክኖሎጂ  በፈለጉት ጊዜና ቦታ ስራ ላይ እንዳያውሉት የሚከለክላቸው ነገር ስለሌለ በአፍሪካና ሌሎችም አካባቢዎች ትልቅ ጥፋትን ሊያስከትል እንደሚችል ፍርሃቱን ገልጿል።

ቴክኖሎጂ በአግባቡ ስራ ላይ ሲውል  ለሰው ዘር ሁሉ ገንቢ የሆነ የእድገት አስተዋጽኦ ማድረግ መቻሉ የማያሻማ ቢሆንም፣ ኃያላኑና ባለጸጎቹ አገሮች ብቻ ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ እንደ ሰው ሰራሽ የአየር ንብረት መቀያየሪያ ያሉ ቴክኖሎጂዎች ግን በኤኮኖሚና በቴክኖሎጂ ገና እያደጉ ባሉት እንደ አፍሪካ ያሉ የዓለም ክፍሎች ብዙ ህዝብን ሊጨርሱ የሚችሉ አደጋዎችን ሊፈጥሩ መቻላቸው ያልተረጋገጠየሴራ ወሬ ወይም “conspiracy theory” ነው ከመባል አልፎ በአደባባይ መነገር መጀመሩ መጽሐፍ ቅዱስ ከብዙ ሺ ዓመታት በፊት በመጨረሻው ዘመን በምድር ላይ ይከሰታሉ በማለት ያስቀመጠልን ማስጠንቀቂያዎች ምን ያህል እውነት እንደሆኑ ያስረዳል። ለምሳሌ ያህል በማቴዎስ ወንጌል ምእራፍ 24 ቁጥር 7 ላይ “ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፣ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፣ እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው ይላል።”  በዮሐንስ ራዕይ ውስጥ በግልጽና በዝርዝር እንደተቀመጠው በሰባቱ ዓመት ታላቁ የመከራ ዘመን ጌታ እግዚአብሔር የሰውን ዘር ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ንስሐ ለመመለስ ታላላቅ መቅሰፍቶች በምድር ላይ እንዲፈጸሙ ይፈቅዳል። ነገር ግን ዛሬ በአደባባይ በግልጽ እየተዘገቡ ያሉትን ዜናዎች ልብ ብለን ካዳመጥን የሰው ልጅ ራሱ ደግሞ በሰራው ቴክኖሎጂ በራስ ወዳድነት፣ በማን አለብኝነትና በግድ የለሽነት የተፈጥሮን ሚዛን በማቃወስ ረሃብን፣ ቸነፈርን እና የምድር መናወጥንም በሰፊው ሊፈጥር መቻሉን እናስተውላለን።


የሰማይና የምድር እንዲሁም የሰው ዘር ሁሉ ፈጣሪና ባለቤት እግዚአብሔር ነው። የሰው ልጅ የተሰጠችውን ይህችን ምድርና ከባቢ አየርዋን በመስማማትና በመተሳሰብ መጠቀም ሲገባው፣ በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸውና በኃይላቸው በመመካት ህዝብን የሚፈጅ፣ የሚያስርብና ለጥፋት የሚዳርግ ራስ ወዳድና እኩይ ተግባሮችን በተፈጥሮ ላይ የሚፈጽሙ ሁሉ በእግዚአብሔር የፍርድ ቀን ለስራቸው መልስ ይሰጡበታል። ለዚህ ነው በዮሐንስ ራዕይ ምዕራፍ 11 ቁጥር 18 ላይ “ምድርንም የሚያጠፉትን ታጠፋ ዘንድ ዘመን መጣ” ተብሎ የተጻፈው። እያንዳንዳችን መረዳቱና እድሉ ያለን ክርስቲያኖች ለሐገር መሪዎች በመጸለይ እና ስንችል ደግሞ በዚህ መልእክት ላይ እንደ ተገለጠው ያሉ የእግዚአብሔርን ሥራ የሚፈታተኑና በህዝብ ላይ እልቂት ሊያመጡ የሚችሉ ነገሮችን መግለጥ፣ መቃወምና በጊዜው እርምት እንዲደረግ ማሳሰብ ግዴታችን ነው። ዓይናችንን ከፍተን የሚካሄደውን እንመልከት፣ ያለነው በዘመኑ መጨረሻ ነው። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልሶ ይመጣል፣ እስከዚያ ግን የክፉውን ስራ ሁሉ በመቃወምና የክርስቶስን የወንጌሉን ብርሃን በማብራት እንጽና። ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...