የመጀመሪያው የሰው ሰራሽ አእምሮ ፖሊስ (ሮቦኮፕ) በዱባይ ስራቸውን ጀመሩ


ባለፈው ሳምንት በላክሁት መልእክት ላይ በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ሰው ሰራሽ አእምሮ (Artificial Intelligence) ዛሬ በሰው ልጆች ከሚሰሩት ስራዎች ውስጥ እስከ 50 በመቶ የሚሆኑትን እንደሚወስዱ የሚናገር ዜናን አያይዤ ነበር። እነዚህ በ AI የሚወሰዱ ስራዎች ደግሞ ማሽኖች መስራት ይገባቸዋል ወይም ሊሰሩአቸው ይችላሉ ብለን የምናስባቸውን እንደ ጽዳት፣ እቃ መጫንና ማውረድ የመሳሰሉትን ብቻ ሳይሆን እኛኑ ራሳችንን የሰው ልጆችን ማስተዳደርም ሊሆን እንደሚችል ጠቆም አድርጌ ነበር። በዚህ በተያያዘው ዜና ላይ እንደምታነቡት ታዲያ የተባበሩት የዓረብ ኤሚሬቶች ዋነኛዋ የንግድ ከተማ ዱባይ የመጀመሪያውን የAI ፖሊስ በስራ ላይ አሰማርታለች። በሚቀጥሉት 13 ዓመታትም ከዱባይ የፖሊስ ሃይል 25 በመቶው በነዚሁ AI ፖሊሶች (ሮቦኮፕስ) እንደሚሆን ብርጋዲዬር ጀነራል ካሊድ ናሲር አል ራዙቂ የሚባሉት የዱባይ ፖሊስ የዘመናዊ ወይም የተራቀቁ አገልግሎቶች ዲሬክተር ጀነራል ተናግረዋል። የሚቀጥለው የሮቦት ሹመት ደግሞ ምን ይሆን?! ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...