የመለከት ድምጽ መጽሔት ቁጥር 8

ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ ለዘላለምም ያው ነው ብለን ካመንን በሐዋርያት ዘመንና ከነሱም በኋላ በነበረችው እውነተኛይቱ ቤት ክርስቲያን ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ ዛሬም እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑትን በመንፈስ ቅዱስ ይሞላቸዋል ወይ?
ዛሬም እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተአምራትን ይሰራል ወይ? በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመንም እንደ ትንቢት ያሉ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አሉ? ይሰራሉ? ዛሬም እግዚአብሔር ነቢያትን ይልካል? የሚሉ ጥያቄዎች በብዙ መድረኮች ይነሳሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ለነዚህ ጥያቄዎች ሙሉና የማያሻማ መልሶች አሉት። እነዚህንና ከነዚህ ጋር በተያያዙ ሃሳቦች ላይ ትምህርቶችንና ትንተናዎችን ይዛ የመለከት ድምጽ ቁጥር 8 ዛሬ ወጥታለች።በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የዘለዓለም ሕይወትን ያገኙ ቅዱሳን ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ሙላትንና የእርሱን ድንቅ ስራዎችን በተመለከተ ትምህርትና መጽናናት እንዲያገኙበት ጸሎቴ ነው። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ገና ያልተቀበሉት ወገኖቼም ደግሞ የሰው ዘር ብቸኛ የመዳን ተስፋ የሆነውን ይህን ጌታ እንዲቀበሉት የልቤ ምኞችና ጸሎት ነው። እግዚአብሔር ይባርካችሁ።
ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...