የመለከት ድምጽ መጽሔት ቁጥር 12 ዛሬ ወጥታለች - ዋና ርዕስ "ይህን ዘመን የማትመረምሩ እንዴት ነው? " ሉቃስ 12፡56

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር በነበረባቸውና ወንጌልን በሰበከባቸው ዓመታት ሊያዳምጡት ይመጡ የነበሩትን ህዝብ ማስተማር ብቻ ሳይሆን ጥያቄዎችንም ይጠይቃቸው ነበር። የጥያቄዎቹም ዓላማ ሰሚዎቹ የሚያዩትንና የሚሰሙትን እንዲያስተውሉና በመካከላቸው የተገለጠውን እግዚአብሔር ወልድን በማወቅ ወደ ዘለዓለም ሕይወት እንዲመጡ ለማድረግ ነበር። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ
ከጠየቃቸው ከእነዚያ ጥያቄዎች አንዱ በሉቃስ ወንጌል ምእራፍ 12 ቁጥር 56 ላይ ይገኛል። ይህ ጥያቄ ከዛሬ ሁለት ሺህ ዓመት በፊት ለነበሩትና ክርስቶስን ይሰሙ ለነበሩ ሰዎች እንዳስፈለገው ሁሉ በዚህ ዘመን ለምንኖር ለእኛም ያስፈልጋል። ይህ የእኛ ዘመንስ ምን ዓይነት ነው? ወዴት እያመራ ነው? ፍጻሜውስ ምን ይሆን? የሚሉትን ጥያቄዎች ልንጠይቅና በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ለነዚህ ጥያቄዎች በቅድሚያ በነቢያት፣ በጌታ በራሱና በሐዋርያት በትንቢት የተሰጡትን መልሶች ልናጤን ይገባል። ዛሬ የወጣችው የመለከት ድምጽ 12 ቁጥር ይህን ጥያቄ በአጭሩ በማንሳት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት እጅግ እየተቃረበ መሆኑን ለማስረዳት ትሞክራለች። መልካም ምንባብ።
ወንድማችሁ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...