የሰው ልጅ መንፈሳዊ ታሪክ ምስጢር ከኖኅ እስከ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት

የሰው ልጅ መንፈሳዊ ታሪክ ምስጢር ከኖኅ እስከ ባቢሎን፣ ከባቢሎን እስከ እስራኤል፣ ከእስራኤል እስከ ቤተ ክርስቲያን መመስረት፣ ከቤተ ክርስቲያን እስከ እስራኤል መሰብሰብና እስከ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት

ይህም ሊሆን ሲጀምር ቤዛችሁ ቀርቦአልና አሻቅባችሁ ራሳችሁን አንሱ። ሉቃስ 21:28
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የዳግም ምጽዓቱን መቃረብ እንደሚያመለክቱ ከሰጣቸው ምልክቶች ውስጥ አንዱንና ትልቁ በዓለም ላይ የሚታየው ሁኔታ ከጥፋት ውኃ በፊት ቀደም ብሎ ኖህ ወደ መርከብ እስገባበት ቀን ድረስ በምድር ላይ የነበረውን መንፈሳዊ፣ ሞራላዊ፣ ህብረተሰባዊ፣ ፖለቲካዊና ኤኮኖሚያዊ ውድቀትን እንደሚመስል ነበር። እነዚህ ነገሮች ደግሞ በቀደሙት መልእክቶች ላይ ተመልክተናል። ይህን የዛሬውን መልክት ለመረዳት ደግሞ እነዚያን ስለ ኖኅ ዘመን የተማርናቸውን ማንበብ ያስፈልጋል።
በኖኅ ዘመን ከልኩ አልፎ የገነፈለው መንፈሳዊና ሞራላዊ ውድቀት እጅግ የከፋና ከመቤዠትም ያለፈ ስለነበር ጌታ አምላክ የዚያን ዘመኑን ዓለም በውሃ አጠፋ። ጌታ አምላክ ከዚያ ጥፋት በኖህ መርከብ አማካይነት የዳኑትን 8 ሰዎችና የተመረጡ እንስሳት ባርኮ ምድር ሁሉ እንደገና በሕያዋን ፍጥረታት ተሞላች። እጅግ የሚያሳዝነው ግን ከዚያ ከጻድቅ ሰው ከኖኅ ዘር የወጡት የሰው ልጆችም ቢሆን እንደገና አመጹ። አባቶቻችንና እናቶቻችን ክርስቲያኖች ስለሆኑ ወይም ጻድቃን ስለነበሩ እኛ በነሱ ትኬት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት አንገባም። የኖኅ ልጆች ከሌሎች ከወደቁት ከሰማይ መላእክት ጋር በዓመጽ በመተባበር የፍጥረትን ሁሉ አምላክ እግዚአብሔርን በመተውና “ራሱ ወደ ሰማይ የሚደርስ ግንብ እንስራ” በማለት የልዑል አምላክን ሥልጣንና ሥርዓት የሚጋፋና የሚያፈርስ የዓለም ሥርዓት ለመመስረት በናምሩድ አስተባሪነት ተሰበሰቡ። ይህ ዓመጽ የተፈጸመበትን በሰናዖር (SHINAR) ሜዳ ያለ ስፍራና የተካሄደውን ዓመጽ መጽሐፍ ቅዱስ ባቢሎን ይለዋል። በዚህ በባቢሎን ጊዜ ግን ጌታ እግዚአብሔር የሰዎችና የኔፊሊም ዓመጻ ወደ ፍሬያማነት ደረጃ እንዲደርስ አልፈቀደም። ወደነበሩበት ስፍራ ከመጣና የአካሄዳቸውን የጥፋት አቅጣጫ ከተመለከተ በኋላ ስራቸው ወደግቡ እንዳይደርስ ቋንቋቸውን ደባለቀ፣ የጀመሩትንም ከተማና ሥራ ትተው እንዲሄዱ በምድር ሁሉ በተናቸው። በዘፍጥረት 11 ቁጥር 8 ላይ “እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፣ ከተማይቱንም መስራት ተው።” ይላል። ከብዙ ዘመናት የታሪክና የአርኪዎሎጂ ጥናት በኋላ ያች ስራዋ ሳይጠናቀቅ የተተወች የሰናዖር ሜዳ ከተማ ኤሪዱ (ERIDU) የተባለች መሆኗን እና ይችም ከተማ የሰው ልጆች ከሰሯቸው ከተሞች ሁሉ የመጀመሪያይቱ ልትሆን እንደምትችል የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የታሪክና የአርኪዎሎጂ ተመራማሪዎች ያስረዳሉ።
በባቢሎን ዘመን ጌታ አምላክ ያደረገው የሰዎችን ቋንቋ መደባለቅ ብቻ አልነበረም። ፍላጎታቸው ከሱ በታች የሆኑ ፍጥረታትን፣ ማለትም የወደቁ መላእክትን፣ የነሱን ልጆች አጋንንትንና ሌሎችንም የሰማይና የምድር ፍጥረታትን ማምለክ ስለነበረ ጌታ አምላክ እነሱ ካልፈለጉት በቀጥታ በእርሱ ሥር  ይተዳደሩ ከነበረበት ሥርዓት ስር አውጥቶ እነሱ በመረጡት በሉሲፈርና በወደቁት መላእክቱ አስተዳደር ሥር አደረጋቸው። ይህንንም ሲያደርግ በዚያን ዘመን የነበሩትን ህዝብ በነገዶች መሪዎቻቸው ቁጥር ሰባ (70) ቦታ ላይ በመክፈልና በእያንዳንዱም ላይ የሚያስተዳድሩ የሰማይ መላእክትን በመሾም ነበር። እነዚያ ሰባዎቹን የምድርን ወገኖች የሚያስተዳድሩ የሰማይ መላዕክትም ስማቸው ጠባቂዎች (ወይም WATCHERS) እንደሚባሉ መጽሐፍ ቅዱስ ያሳያል። በዘፍጥረት ምዕራፍ 10 ላይ የተገለጠው የአህዛብ ወይም የምድር ህዝቦች ሊስት ሰባ (70) የጎሳ ወይም የዘር መሪዎችን የያዘ ነው። እነዚህ ሰባዎቹ ነገዶች ናቸው በቀጥታ በጌታ እግዚአብሔር ስር በመተዳደር ፈንታ እነሱ ራሳቸው እንደፈለጉት በወደቀው ኪሩብ በሉሲፊር ስር በነበሩት በጠባቂ መላእክት (WATCHERS) እንዲተዳደሩ የተደረጉት።
በኋላ ከተጠራውና የእግዚአብሔር ርስት ለምትሆነው ለእስራኤል አባት ከሆነው ከአብርያም በስተቀር ከነዚያ ከሰባዎቹ ነገዶች ውስጥ በሰማይ ጠባቂዎች (WATCHERS) ስር ያልተደረገ ማንም ሕዝብ አልነበረም። ኦሪት ዘዳግም 32 ቁጥር 8 ይህንኑ የጌታ አምላክን ውሳኔ እንዲህ ሲል ያስረዳል። “የዱሮውን ዘመን አስብ፥ የብዙ ትውልድንም ዓመታት አስተውል፥ አባትህን ጠይቅ ያስታውቅህማል፣ ሽማግሌዎችህን ጠይቅ ይነግሩህማል። ልዑል ርስታቸውን ለአህዛብ ባወረሰ ጊዜ፣ የአዳምን ልጆች በለየ ጊዜ፣ እንደ እስራኤል ልጆች ቁጥር፣ የአህዛብን ድንበር አቆመ። የእግዚአብሔር እድል ፈንታ ህዝቡ ነው፥ ያዕቆብም የርስቱ ገመድ ነው።” እነዚያን የሰማይ ጠባቂዎች (WATCHERS) ወይም በሰይጣን ሥር ሆነው አህዛብን እንዲያስተዳድሩ የተመደቡትን የወደቁትን መላእክትን እና ልጆቻቸውን ኔፊሊምን ነው የሰው ልጆች የአገራችን አማልክት እያሉ ያመልኩአቸው የነበረው። ለምሳሌ የሞዓባውያን አምላክ ኪሞሽ፣ የአሞናውያን አምላክ ሞሎክ፣ የባቢሎን አማልክት ማርዱክ፣ በዖልና ብልጣሶር ወዘተ ነበሩ። ለዚህም ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብዙ ስፍራ ላይ አገሮችንና ህዝቦችን የሚገዙ በአየር ላይ ሥልጣን ያላቸው ገዢዎች እንዳሉ የሚናገረው። ለምሳሌ ዳንኤል 4:13 ፣ 4:17 ፣ 4:23 ፣ ዳንኤል 10:13 እስከ 21፣ ማቴ 4:9፣ ሉቃስ 4:6፣ ኤፌሶን 6:12 ፣ ዮሐንስ 14:30 ፣ ዮሐንስ 12:31 ። ለዚህም ነው ዲያብሎስ ጌታ ኢየሱስን በምድረ በዳ በፈተነው ጊዜ የዓለምን መንግስታትና ክብራቸውን ለጌታ ለኢየሱስ አሳይቶ ይህ ሁሉ የኔ ነው፣ ከሰገድህልኝ ላንተ እሰጥሃለሁ ያለው። ዲያብሎስ ይህንን ሲናገር ታዲያ ከመጀመሪያውም የዓለም መንግስታት በሱ ስር እንዲሆኑ የሰጠው ያ ሊፈትነው የቀረበው ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን አላወቀም ነበር። ለዚህ ነው ሐዋርያው ጳውሎስ የአሁኑ ዘመን የምድር ገዥዎች የእውቀትን ራስ አላወቁትም። ቢያውቁ ኖሮስ አይገድሉትም ነበር ያለው። ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰይጣንን ድል የነሳው በመስቀል ሞቱ ነው። ሰይጣንና የሚከተሉት የወደቁት መላእክቱ በባቢሎን የሰውን ዘር እንዲያስተዳድሩ ስለተመደቡም ነው ጌታ ኢየሱስ ሰይጣንን የዚህ ዓለም ገዢ ብሎ በወንጌል ላይ የጠራው።  ጌታም በመጨረሻ ወደ መስቀሉ ሲሄድ የዚህ ዓለም ገዢ ተፈረደበት ወይም ተጣለ አለ። ለዚህም ነው መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ስለ ተቀበሉ ሰዎች ሁሉ ሲናገር “እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፣ ቤዛነቱንም እርሱም የኃጢዓትን  ሥርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግስት አፈለሰን።” ቆላስይስ 1:13 የሚለው።
ጌታ አምላክ የአህዛብን የልባቸውን ዝንባሌና ፍላጎት፣ እንዲሁም በተግባር በተደጋጋሚ ያደረጉአቸውን ምርጫዎች ከተመለከተ በኋላ የፈለጉትን ሰጣቸው እንጂ እሱ ራሱ ደግሞ የሁሉም አምላክ ነውና እነዚያ ጠባቂዎች (WATCHERS) የተባሉትና በሉሲፈር ስር የሚተዳደሩት መላእክት ደግሞ እንደፈለጋቸው እንዳይፈነጩ ለስልጣናቸው ገደብን አደርጎለታል። ለምሳሌ አንድ ሰው የነዚህን የጠባቂዎችን የክፋት መንገድ አልከተልም ብሎ እና ጌታ አምላክን ወዶ በጽድቅ ቢመላለስ ጠባቂዎቹ ያንን ሰው እነሱ እንደሚፈልጉት እንዲሆን ሊያስገድዱት አይችሉም። ከጌታ አምላክ ካልተፈቀደላቸው በቀር መከራና ፈተናንም እንኳን ሊያመጡበት አይችሉም። ይህንን በተመለከተ የኢዮብን ታሪክ በሚገባ ማስተዋል ያሻል። ኢዮብ ላይ የደረሰውን መከራ ብቻ ሳይሆን፣ ከመከራው በፊት ጌታ አምላክ በሚመራው በሰማይ ጉባኤ የተካሄደውን የክስና የፍርድ ስርዓት በተመለከተ በኢዮብ ምእራፍ 1 ቁጥር 7 እስከ 12 እና ምእራፍ 2 ከ1 እስከ 6 ያለውን በሚገባ እናስተውል። ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር በአማልክት ላይ አአምላክ ነው፣ በአማልክት ጉባኤ መካከል ይፈርዳል የሚለው። ለምሳሌ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 82 ቁጥር 1 እስከ 8ን አንብቡ። ስለዚህ አህዛብን እንዲገዙ ያስቀመጣቸውን ሰማያዊ ጠባቂዎችንም (WATCHERS) የሚገዛውና የሚፈርድባቸው የእስራኤል አምላክ፣ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር ነው። በዚህ በመዝሙረ ዳዊት 82 ላይና በሌሎችም ብዙ ስፍራዎች እንደምናነበው እነዚያ ጠባቂዎች ደግሞ በሚገባ ስላላስተዳደሩ፣ ጻድቃንን በማሰቃየት ለአመጸኞች ስለፈረዱና ራሳችውም በሙስና ውስጥ ስለተዘፈቁ ምንም እንኳን አማልክት ቢሆኑም እንደሚፈረድባቸውና እንደሚሞቱ ይናገራል። የእሳት ባህርም የተዘጋጀው ለነዚህ ክፉ ገዢዎችና ለአለቃቸው ለዲያብሎስ ነው። በነዚህ ላይ ነው ሐዋርያው ጳውሎስ “በመላእክት ላይ እንኳን እንድንፈርድ ዘንድ እንዳለን አታውቁምን? “ ብሎ ለቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን የጻፈው። 1ኛ ቆሮ 6:3ን ተመልከቱ። እነዚህ ጠባቂዎች ናቸው ዛሬም ቢሆን የምድርን አህዛብ ከመንግስታት ጀርባና ከበላያቸው ሆነው  የሚገዙትና የሚያስቷቸው። ለዚህ ነው የእግዚአብሔር ቃል ለመንግስታት መሪዎችና በስልጣን ላይ ላሉ ሁሉ ጸልዩ ብሎ የሚያዝዘን። 1ኛ ጢሞቲዎስ 2:2ን ተመልከቱ። እነዚህ የአሁኑ ዓለም ገዢዎች ሳይወዱ በግድ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ይፈጽማሉ። ብዙ ጊዜ ግን በዓመጽ የራሳቸውን ክፉ ሃሳብ ለማድረግ ሲሞክሩና የሰው ልጅም በአካሄዱና በምርጫው ሲተባበራቸው ምድር ቀውስ ውስጥ ትገባለች። ለዚህ ነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናንተ የምድር ጨውና የዓለም ብርሃን ናችሁ ብሎ ለደቀመዛሙርቱና ክርስቲያን ነን ለምንል ሁሉ ያስተማረው።
አህዛብን በጠባቂዎች ስር ያኑር እንጂ ጌታ አምላክ ለሱ ለራሱ ደግሞ እስራኤልን አስቀርቶ ነበር። አብርሃምን ወደራሱ ጠርቶና ፈትኖ ቃል ኪዳን ከገባለት በኋላ እውነተኛና መንፈሳዊ የሆነው የአብርሃም ዘር የእግዚአብሔር ርስት ሆነ። ለዚህ ነው ጌታ አምላክ እስራኤልን ከግብጽ ባርነትና ከፈርዖን ስልጣን ስር ነጻ ያወጣው። የግብጽ ፈርኦኖች አማልክት ናቸው ተብለው የሚመለኩና ብዙዎቹም ከኔፊሊም ጋር የተያያዘ ሰማያዊ ዘር አለን የሚሉ ነበሩ። ለዚህ ነው የግብጻውያን መሪዎች የእስራኤልን ህዝብ የበኩር ልጆች ገና ሲወለዱ በመግደልና ከዚያም የተረፉትን ወደ አባይ ወንዝ በመጣል ሊያጠፉአቸው የተነሱት። ለዚህ ነው ጌታ አምላክ ራሱ ከእስራኤል ልጆች ጋር በመውጣትና የፊቱን መልአክ በመላክ እስራኤላውያን በከነዓን ምድር የነበሩትን የኔፊሊምን ዘር እያጠፉ ምድሩን እንዲወርሱ የረዳቸው። በጌት የነበረውና ዳዊት የገደለው ጎልያድ የኔፊሊም ዘር ቅሪት ነበር። ኢያሱ ምድሩን ለእስራኤል ሲያወርስ ሳያጠፋቸው የቀሩ የኔፊሊም ዘሮች ሸሽተው የሰፈሩባቸው ቦታዎች  ጌት፣ ጋዛና አዛጦን ነበሩ። እስራኤል በልዑል አምላክ ስር በቀጥታ የሚተዳደሩ ብቸኛና ቅዱስ ሕዝብ፣ የንጉስ ካህናት፣ ምርጥ ህዝብና ለአህዛብ ብርሃን እንዲሆኑ የተጠሩ ስለነበሩ ነው ከሌሎቹ ከአካባቢያቸው አህዛብ ጋር በአምልኮ፣ በጋብቻና በአኗናሯቸውም ሳይቀር እንዳይደባለቁ የታዘዙት። ያንን ካደረጉ ሳይወዱ በግድ እነዚያን አህዛብን በሚገዙት ጠባቂዎች ስልጣንና የአጋንንት አምልኮ ኃይል ስር እንደሚወድቁ ጌታ አስጠንቅቋቸው ነበር። ይህ እጅግ ታላቅ የሆነ መንፈሳዊ ምስጢር እንጂ የዘረኝነት ወይም የአንድ ዘር ከሌላው የመሻል ጉዳይ አይደለም። ጌታ አምላክ ራሱ ይህንን ለእስራኤል በግልጽ ሲነግራቸው የመረጣቸው ከአህዛብ ሁሉ ይልቅ ሰለሚሻሉ ወይም በቁጥር ስለበዙና ኃይለኛ ስለሆኑ ሳይሆን ከአባቶቻቸው ጋር ስላደረገው ቃል ኪዳን የተነሳ ስለወደዳቸው መሆኑን አስታውቆአቸዋል። ዘዳግም 7 ቁጥር 7 እና 8።
እስራኤል ማለት በአካል የያእቆብ ልጆች የሆኑትን የአስራ ሁለቱን ነገዶች ዘር የሚጠቅስ ሲሆን በመንፈስ ደግሞ የአብርሃምን የእምነቱን ፍለጋ የሚተከተሉት ሁሉ ናቸው። ሮሜ 4:12 በብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔር ራሱ ነበር እስራኤልን በቀጥታ የሚያስተዳድራቸው። ለዚህ ነው እስራኤል የበኩር ልጄ ነው ብሎ ጌታ የተናገረው። ዘጸዓት 4:22። ለዚህ ነው እስራኤልን ለማዳን ጌታ አምላክ ማንኛውንም ህዝብና  ገዢ ያንበረክክ የነበረው። ማንኛውም የአብርሃም ዘር የአባታቸውን የአብርሃምን የእምነቱን ፍለጋ በመከተል የአብርሃምን፣ የይስሐቅንና የያዕቆብን አምላክ ካመለኩና ከተከተሉ፣ ከሌሎች የአህዛብ አማልክት አምልኮና ተጽእኖ ከተጠበቁ የእግዚአብሔር ሕዝብና ርስት ናቸው። አንድ ሰው በስጋ የአብርሃም ዘር ሆኖ የእስራኤልን አምላክ ካላመነና ካልታዘዘ መንፈሳዊ እስራኤል አይደለም። በዘሩ የአብርሃም ዘር ያልሆነ ሰው ደግሞ በእውነትና በመንፈስ አብርሃም ያመነውንና የታዘዘውን አምላክ ቢያምን፣ ቢታዘዝና ቢከተል በስጋ እስራኤላዊ ባይሆንም እንኳን በመንፈስ ግን የአብርሃም ልጅ ይሆናል። ይህ በብሉይ ኪዳን ዘመንም ሆነ በአዲስ ኪዳን እውነት ነው። ለምሳሌ የኢያሪኮይቱ ጋለሞታይቱ ረዓብና ሞአባዊቷ ሩት ዋና ዋና ምሳሌዎች ናቸው። እጅግ ብዙ እስራኤላውያን ጌታ አምላክን ታዝዘው ቢኖሩም ብዙዎቹ፣ በተለይም ደግሞ መሪዎቻቸው እግዚአብሔርን ስላልታዘዙ፣ በመጨረሻም ደግሞ በአካል በመካከላቸው የተገለጸውን የእግዚአብሔርን ልጅ፣ እውነተኛውን መሲሕ ኢየሱስ ክርስቶስን በአገር አቀፍ ደረጃ ስላልተቀበሉት ከእግዚአብሔር ጋር የገቧቸውን ቃል ኪዳናት አፈረሱ። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳና ካረገ በኋላ ያመኑት ደቀመዛሙርት (እስራኤላውያን የሆኑ) ወንጌልን ለምድሩ ሁሉ ስለሰበኩ ብዙ እስራኤላውያን በመሲሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ቢያምኑም በአገር ደረጃ ግን እስራኤል ስላልተቀበሉትና ከጌታ ትንሳኤ በኋላ የተሰጣቸውንም  40 ዓመት የንስሃ ጊዜ ስላልተጠቀሙበት በሮማዊው ቲቶ (TITUS) ይመራ የነበረው የአህዛቡ የሮም ሰራዊት ኢየሩሳሌምን አፈራርሶ፣ የእስራኤል መንግስትነት ለጊዜው አብቅቶ፣ የቀሩት አይሁድ በምድር ሁሉ ተበተኑ። ወንጌልን በመጀመሪያ ለምድር ሁሉ ያበሰሩትም እስራኤላውያንና አይሁድ የነበሩ ሐዋርያት መሆናቸውን አንዘንጋ። ጳውሎስ በሮሜ መልእክት ላይ እንደጻፈውና ነቢያትም ከዚያ በፊት እንደተናገሩት እስራኤል ምንም እንኳን የቃል ኪዳን ልጆችና የተስፋው ቃል ወራሾች ቢሆኑም፣ እንደ አገር መሲሁን ኢየሱስን ባላመቀበላቸው መንፈሳዊ ድንዛዜ ሆነባቸው። ሮሜ ምእራፍ 9፣ 10 እና 11ን ተመልከቱ። ስለዚህም ከዚህ መንፈሳዊ ድንዛዜ እስኪነሱ ድረስ ወንጌል ለአህዛብ ሁሉ ባለፉት ሁለት ሺ ዓመታት ተሰበከ። በመጨረሻው ዘመን ግን እስራኤል ከመንፈሳዊ ድንዛዜአቸው ተነስተው ጌታ ኢየሱስን እንደሚቀበሉት ነቢዩ ዘካርያስ ጽፎአል። ዘካርያስ 12:10 ስለዚህ እግዚአብሔር እስራኤልን በትኖ በቤተ ክርስቲያን ተክቷል የሚለው ትምሕርት የተሳሳተና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነ ነው።
ጌታ ኢየሱስ ስለዳግም ምጽዓቱ ከሰጠን ምልክቶችም አንዱ “በለስ ስታቆጠቁጥ ጫፍዋም ሲለሰልስ ያን ጊዜ በጋ እንደቀረበ ታውቃላችሁ” ማቴ 24:32 የሚለው ስለ እስራኤል እንደ አገር ተመልሶ መመስረት የተነገረ ትንቢት ነው። በብሉይ ኪዳንም ብዙ ነቢያት እስራኤል ከመበተን በኋላ እንደገና አገር እንደምትሆንና በእስራኤልም መዳን ለዓለም ሁሉ የወንጌል መሰበክ ተደምድሞ የጌታ መንግስት በምድር ላይ እንደምትገለጥ ተናግረዋል። ታዲያ በ70 ዓም ኢየሩሳሌም ስትፈርስ ተበትኖ የነበረው የአይሁድ ህዝብ ከ2000 ዓመታት ያህል በኋላ ከምድር ሁሉ ተሰብስቦ ያች የጥንቷ እስራኤል ጌታ አምላክ ለአብርሃም ቃል በገባለት መሰረት ምድር ላይ እንደገና አገር ሆና የተመሰረተችው ባለፈው ምዕተ ዓመት በ1948 እ ኤ አ ነበር። ይህ አስገራሚና አስደናቂ ተአምራት ጌታ ኢየሱስ ዳግም የሚመለስበት ዘመን መቃረቡን ያለጥርጥር ከሚያስረዱን ክስተቶች አንዱና ዋነኛው ነው። የዛሬዋ እስራኤል ዜጎች ብዙዎቹ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አያምኑም። የሚያምኑ ብዙ ግን አሉ። እግዚአብሔር ሕዝቡን እስራኤልን እንደገና ሰብስቦ አገሪቱ የተመሰረተበትን ዋና ዋና ምክንያቶች ከመጽሐፍ ቅዱስ ስናስተውል የሚከተሉትን አምስት ነጥቦች ማመልከት እንችላለን 1ኛ) እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባውን ቃል ኪዳን እስከመጨረሻ የሚጠብቅ አምላክ መሆኑን ለማሳየት ነው 2ኛ) እስራኤል በመጀመሪያ ለነሱ የመጣውን ወንጌልን እንደገና እንዲሰሙና በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው እንዲድኑ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው 3ኛ) አህዛብ ሁሉ የእስራኤል አምላክ እሱ ብቻ አምላክ እንደሆነ እንዲያውቁ፣ እንዲያምኑና እንዲድኑም ይሻል 4ኛ) በሰማይም፣ በምድርም፣ ከምድርም በታች ያሉ ሁሉ ስልጣን የእግዚአብሔር ብቻ መሆኑን እንዲያውቁ ነው 5ኛ) በልጁ በክርስቶስ በኩል በዓለም ሁሉ ላይ የሚፈርድበትንና የዘለዓለም መንግስቱን ለመግለጥ ጊዜው መዳረሱን ለማመልከት ነው።
እስራኤል ዛሬ እውን የሆነች አገር ነች። ይህ እውነት የምድር አህዛብ፣ የሲኦል አጋንንትና ግዑዛን ፍጥረታትም ሁሉ ቢያብሩ ሊቀየር የማይችል ነገር ነው። ይህን የማይቀበሉና እስራኤልም በቆዳ ስፋትና በህዝብ ብዛት ትንሽ መሆኗን ተመልክተው  ሊያጠፉአት የሚፈልጉ የምድር መንግስታትና ህዝቦች ቢኖሩም የእግዚአብሔርን ኃይልና የእስራኤልን ታሪክ በሚገባ ያልተገነዘቡ ናቸው ናቸው። ለዚህም ነው ታላላቅ ነን የሚሉትን የዓለም መንግስታት ጨምሮ ብዙ አህዛብ በእስራኤል ላይና በኢየሩሳሌም ላይ እየተነሱ ያሉት። ጠፍታለች፣ ወድማለች፣ ሁለተኛ አትነሳም የተባለች አገርና ሕዝብ ከ2000 ዓመት በኋላ ተሰብስበው አገር መሆናቸውና ይህ ደግሞ በ20ኛው እና በ21ኛው ክፍለ ዘመን መፈጸሙ ራሱ ታላቅ ተአምራትና የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ፍጻሜ መጀመሪያ ነው። ዓይናችን እያየ ትንቢት እየተፈጸመ ነው። የእግዚአብሔር ቃል በሙሉ ይፈጸማል። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልሶ ይመጣል። ስልጣንና መንግስት ሁሉ  ወደባለቤቱ ወደ ልዑል አምላክ ይመለሳል። ለጊዜው ጨለማ ያንዣበበ ይምሰል እንጂ፣ እግዚአብሔርን ለሚፈሩትና በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሚያምኑት ሁሉ የጽድቅ ጸሃይ በክንፎችዋ ፈውስን ይዛ ትወጣለች። ስለዚህ ቤዛችን የሆነው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ በደጅ ነውና አሻቅበን ራሳችንን በማንሳት በደስታ ልንቀበለው ተዘጋጅተን እንኑር።
ዶ/ር በፈቃዱ ብርሃኑ አድማሱ


ኔፊሊም ከየት መጡ? ከሰው ሴቶች ልጆች የወለዷቸው እነዚያ “የእግዚአብሔር ልጆች” የተባሉት እነማን ናቸው? ትምሕርት 6

የኖህ ዘመን እንደነበር የጌታ መምጣትም እንዲሁ ይሆናል፡ ኔፊሊም ከየት መጡ?  ከሰው ሴቶች ልጆች የወለዷቸው እነዚያ “የእግዚአብሔር ልጆች” የተባሉት እነማን ናቸው?  ትምሕርት 6

ባለፉት 5 ትምህርቶች ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓቱ መቃረቡን ሊያሳዩን እንዲችሉ ከሰጣቸው ምልክቶች አንዱን “የኖህ ዘመን እንደነበረ እንዲሁ ይሆናል” የሚለውን ባጭሩ ተመልክተናል። የነዚህ ትምህርቶች ዓላማ እያንዳንዱ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምንም ሆነ የማያምን ሰው የእግዚአብሔር ልጅ፥ እግዚአብሔር ወልድ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ከድንግል ማርያም የተወለደው፣ በመስቀል ላይ የሞተው፣ በሶስተኛው ቀን የተነሳው፣ በአርባኛውም ቀን አርጎ በአብ ቀኝ የተቀመጠው በእርግጥም የአማልክት አምላክ፣ የነገስታት ንጉስና የጌቶችም ሁሉ ጌት መሆኑን፣  ተመልሶም እንደሚመጣ፣ በኃጥዓንና በጻድቃን ላይ እንደሚፈርድ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረውን እውነት በአንድ ትንሽ ማስረጃ ለማቅረብ ነው።

እግዚአብሔር ወልድ የኛን የሰዎችን ሥጋ ለብሶ የመጣበት ዓላማ እኛን በኃጢዓታችን የጠፋነውን ሰዎች ከዘለዓለም ሞት ለማዳን ነው። ኃጢዓት ደግሞ ሥርና መሰረት አለው። በእርግጥ እያንዳንዱ ሰው መልካምንና ክፉን የመለየት እንዲሁም ደግሞ ጽድቅንና ኩነኔን ለመምረጥ ከፈጣሪ የተሰጠ ችሎታ ቢኖረውም፣ ኃጢዓትን ወደዚህ ዓለም ያገባው በልዑል አምላክ ዙፋን ዙሪያ እንዲያገለግሉ ከተፈጠሩት ሰማያዊ ፍጡራን (በተለምዶ መላእክት ከምንላቸው) አንዱ ሉሲፈር የሚባለው ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ሰማያዊ ፍጡራን ብዙ ዓይነት እንደሆኑ ያስተምራል።፤ ለምሳሌ ኪሩቤል፣ ሱራፌል፣ ሊቃነ መላእክት፣ አለቆች፣  ሥልጣናት፣ ገዢዎች፣ መላዕክት ወዘተ። ሰይጣን፣ ዲያብሎስ፣ የቀደመው እባብና ዘንዶ ወዘተ በመባል በመጽሐፍ ቅዱስ የሚጠራው ሉሲፈር (በእብራይስጥ  רשָׁ֑חַ ןבֶּ ללֵ֣הֵי ወይም ሂሌል ቤን ሻኻር ወይም በአማርኛ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ተብሎ በኢሳይያስ 14:12 ላይ የተጠቀሰው) የልዑል እግዚአብሔርን ዙፋን ከሚጋርዱት ኪሩቤል አንዱ ነበር ሕዝቅኤል 28:14። የተሰጠው ታላቅ ውበት፣ ክብር፣ ግርማና የአገልግሎት ስፍራ አልበቃ ብሎት የልዑል አምላክን ቦታ የተመኘ ይህ ፍጥረት በትእቢቱ ምክንያት የልዑል አምላክ ዙፋን ካላበት ሰማይ ክብሩን እና ቦታውን ተገፍፎ በተጣለ ጊዜ ከሱ ጋር በዓመጽ የተባበሩ ሌሎች  እጅግ ብዙ የሰማይ ፍጥረታትም አብረውት ተጥለዋል።  ከዚህ ከክብሩ መጣል ጋር በተያያዘ ቅንዓትና ቁጣ ተነሳስቶ ነው ይህ ክፉ ጠላት በልዑል አምሳል የተፈጠረውን ሰውም የውድቀቱ ተካፋይ እንዲሆን በማታለል ወደ ኃጢዓት እንዲገባ ያደረገው። ታዲያ ዕባቡ (ሰይጣን) በኤደን ገነት የጀመረውን ሰውን የማሳሳትና የማጥፋት ሥራ በኤድን ገነት አላቆመም። ቃየን በወንድሙ ላይ ተነሳስቶ ንጹሁን ወንድሙን አቤልን ንዲገድለው ያነሳሳው ሰይጣን ነበር። ጌታ ኢየሱስም ሊገድሉት የሚፈልጉትን የአይሁድ መሪዎችን እናንተ የአባታችሁን (የሰይጣንን) ፈቃድ ልትፈጽሙ ትሻላችሁ እርሱ ነፍሰ ገዳይ ነውና ያለበት አንዱ ምክንያትም ይኽው ነው።

ሰይጣን በኤደን ገነት የጀመረውን እግዚአብሔርን የመቃወምና የሰውን ዘር የማጥፋት ሥራውን በኖህ ዘመንም ቀጥሎአል። ለዚህ ነው የሱ ተከታዮች የሆኑ የወደቁ መላእክት የተመደበላቸውን የሰማያዊ ፍጥረታት ክልል በመጣስ ወደ ምድር ወርደው ያለ አግባብ የሰውን ሴቶች ልጆች በመውሰድና የተከለከለ ግብረ ሥጋ ግንኙነት በመፈጸም ኔፊሊምን የወለዱት። እነዚህ ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 6 “የእግዚአብሔር ልጆች“ የሚላቸው መላዕክት ስማቸው ማን እንደነበርና ቁጥራቸውም ስንት እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ አይናገርም። ሌሎች አዋልድ ተብለው የሚቆጠሩ መጻህፍት ግን ቁጥራቸውን፣ ስማቸውን፣ የመሪዎቻቸውን ስሞች፣ ወደ ምድር የወረዱበትን ስፍራ፣ በምድር ላይ ያደረሱትን በደልና ጥፋት እንዲሁም ፍጻሜያቸውን በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎችን ይሰጣሉ። ከእነዚህም መጻህፍት ሶስቱ መጽሐፈ ሄኖክ፣ የያሻር መጽሐፍና የኢዮቤልዩ መጽሐፍ የሚባሉት ናቸው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና ሌሎችም ጥቂት አብያተ ክርስትያናት መጽሐፈ ሄኖክን የመጽሐፍ ቅዱስ አካል አድርገው ይቀበሉታል። የያሻር መጽሐፍ ደግሞ በግልጽና በውስጠ ታዋቂነትም በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ በብዙ ስፍራዎች ላይ ተጠቅሶ እናገኘዋለን፤ ለምሳሌ በኢያሱ 10:13፣ 2ኛ ሳሙኤል 1:18 እና 2ኛ ጢሞቲዎስ 3:8። በፊት በቀረቡት ትምህርቶች ላይ እንዳቀረብኩት፣ የጌታ ኢየሱስ ደቀመዛሙርትና ሐዋርያት እንዲሁም ከነሱ በኋላ የመጡት ቅዱሳን፣  የእነዚህን መጻህፍት መልእክት ማወቅ ብቻ ሳይሆን አንዳንዶቹን መረጃዎቻቸውንም በቀጥታና በተዘዋዋሪ በአዲስ ኪዳን መልእክቶቻቸው ውስጥ ጠቅሰዋቸዋል። ለምሳሌ 2ኛ ጢሞቲዎስ 3:8 ፤ 2ኛ ጴጥሮስ 2፤4 ፤ የይሁዳ መልዕክት ቁጥር 14 እና 15። የኔፊሊምን ታሪክና ማንነት ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ በቂ ነው። የነዚህንም መጻህፍት መረጃ እንደ እግዚአብሔር ቃል አድርገን መውሰድ አንችልም።

እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት አዋልድ ተብለው የሚጠሩ መጻህፍት ከጥፋት ውኃ በፊት ወደ ምድር የወረዱት የወደቁት መላዕክት ሁለት መቶ ያህል እንደነበሩ፣ የወረዱበት ስፍራም በአርዲስ የተራሮች ሰንሰለት ውስጥ የሚገኘው ሄርሞን (በአማርኛ አርሞንኤም) የሚባለው እንደሆነ ይናገራሉ። ይህ ተራራ ዛሬ በእስራኤል፣ በሊባኖስ፣ በዮርዳኖስና በሶሪያ ድንበር አካባቢ ይገኛል። የአካባቢው ስምም ዛሬ የጎላን ኮረብታማ ስፍራ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በእስራኤል፣ በሊባኖስና በሶሪያ መካከል ላለው መሬትን የተመለከተ ያለመግባባት ዋና መንስኤ ነው። እኩይ ተግባራቸውን መፈጸም ከመጀመራቸው በፊት እነዚያ የወደቁት መላእክት በተራራው ላይ ስለ ተማማሉበት፣ ስሙንም ሂርሞን ያሉት እነሱ ናቸው ብሎ መጽሐፈ ሔኖክ ይናገራል። የብሉይ ኪዳንን ታሪክ ብንመለከት ደግሞ ይህ አካባቢ የባሳን ንጉስ ዐግ የተባለው ከኔፊሊም ወገን የቀረ የመጨረሻው ግዙፍ ፍጥረታት ቅሪት ይገዛቸው የነበሩ 60 የኔፊሊም ዘሮች (ራፋይም) ከተማዎች የነበሩበት አካባቢ ነው። ዘዳግም 2 ቁጥር 8 እስከ 17 አንብቡ። በአዲስ ኪዳን ዘመን በዚህ ተራራ ላይና ከስሩ በምትገኘው በፊልጶስ ቂሳርያ ከተማ አጠገብ ጌታ ኢየሱስ የተናገራቸው ቃላትና በተራራው ላይ ክብሩን መግለጹ ሰይጣንና እነዚያ ዓመጸኞች መላእክት የሰሩትን ስራ ለማፍረስ መምጣቱን የሚያመላክቱ ነበሩ። ማቴዎስ 16:13 እስከ 28 እና ማቴዎስ ም 17 ከቁጥር 1 እስከ 21ን አንብቡ። የዲያብሎስን ስራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጸ ተብሎ በሐዋርያው ዮሐንስ የተጻፈው ቃል ዲያብሎስ ምን ያህል በተወሳሰበና በረቀቀ መንገድ የሰውን ዘር ለመበከልና ለማጥፋት እንደጣረና ዛሬም እንደሚጥር የሚያሳይ ጥልቅ መረዳትን የሚጠይቅ ቃል እንጂ ሰይጣን በኤደን ገነት ያደረገውን አንድ ክስተት ብቻ የሚመለከት አይደለም።

ብዙዎቻችን ስለመላእክት ያለን አስተሳሰብ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሰረተ አይደለም። የብዙዎቻችን ሃሳብ እንዲያውም ከሰዓሊዎች ፈጠራ ወይም ከፊልሞች ወይም ከአፈታሪክ የተወሰደ ነው። መላእክት  ክንፍ ያላቸው፣ በብርሃን ተከበው በአየር ላይ የሚንሳፈፉ የዋህና ምንም ክፉም ሆነ በጎ የማይሰሩ ትንንሽ ህጻናት እንደሆኑ የምንገምት ብዙ ነን። በመሰረቱ በአማርኛ መልአክ የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለተጠቀሱት ብዙ ዓይነት ሰማያዊ ፍጥረታት ሁሉ በድምር የተሰጠ ስም ነው። የዚህ ቃል የዕብራይስጡ እኩያ מַלְאַךְ  (መላአክ) ወይም የግሪኩ ἄγγελόν (አንኼሎስ) የሚለው ነው። የነዚህ የእብራይስጥ እና የግሪክ ቃላት ዋና ሃሳብ መልእክተኛ ማለት ሲሆን መልእክትን ከእግዚአብሔር ላመጡ (ለሚያመጡ) የሰማይ ፍጥረታት ሁሉ ያገለግላል። ዋነኛ የአገልግሎት መደባቸው መልእክትን ማምጣት ያልሆነ ሌሎች ብዙ ሰማያዊ ፍጥረታት እንዳሉ ግን መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል። ለምሳሌ ኪሩቤል (የጌታን ዙፋን የሚጋርዱ)፣ ሱራፌል (የጌታን ቅድስና ሊትና ቀን ሳያቋርጡ የሚያውጁ)፣ ስልጣናት (በባህር፣ በውኃ፣ በእሳት፣ በነፋሳት ላይ ሥልጣን ያላቸው)፣ ኃይላት፣ ገዢዎች (የተለያዩ አገሮችንና ህዝቦችን የሚገዙ ፥ ለምሳሌ ገብርኤል ወደ ዳንኤል እንዳይደርስ የተዋጋው የፋርስ መንግስት አለቃ) ወዘተ።

ሌላው መላእክትን በተመለከተ ብዙዎቻችን የምንዘነጋው ነገር መላእክት በሁለት እንደሚከፈሉ ነው ። ሰይጣንን ተከትለው ከክብራቸው የተጣሉ መላእክት አሉ። ነገር ግን ጌታ አምላክን በታማኝነት የሚያገለግሉት ደግሞ ካመጹት ይልቅ በቁጥር እጅግ የሚበዙ ቅዱሳን መላእክት አሉ። የዮሐንስ ራዕይ የወደቁት መላእክት ከጠቅላላው 1/3ኛ ብቻ እንደሆኑ በምዕራፍ 12 ቁጥር 3እና 4 ላይ ያመለክታል። ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ መላእክትን በተመለከተ የተጻፉትን ነገሮች ስናነብ ስለየትኞቹ እንደሆነ መለየት ያስፈልጋል። ለምሳሌ ጌታ ኢየሱስ ስለጋብቻ ሲያስተምር ሳለ፣ ከሞት የተነሱ ቅዱሳን እንደ ሰማይ መላዕክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፣ አይጋቡምም ብሎ ያስተማረው ስለ ቅዱሳን መላእክት ነው። ጌታም አያገቡም፣ አይጋቡምም አለ እንጂ አካል የላቸውም ወይም ማግባት አይችሉም አይደለም ያለው።

ይህንን ክፍል በሚገባ ያልተረዱ ሰዎች ታዲያ መላእክት ሰውነት የላቸውም፣ ሊያገቡ ወይም ፍትወተ ስጋ መፈጸም ስለማይችሉ ከሰዎች ሴቶች ልጆች ጋር ዘራቸውን አደባልቀው ኔፊሊምን ሊወልዱ አይችሉም ይላሉ። በእርግጥ ቅዱሳን መላዕክት ጌታ አምላክ በመደበላቸው የክብር ስፍራ ስለሚኖሩና ስለማይሞቱም ዘራቸውን ለመተካት ሲሉ ሚስት ማግባት ወይም ልጅ መውለድ አያስፈልጋቸውም። ስለዚህም አያገቡም፣ አይጋቡምም። ከወደቁት መላእክት አንዳንዶቹ ግን የጌታን ስርዓት ጥሰው እንግዳ ስጋን በመከተል ዓመጻን እንዳደረጉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ያስተምራል።

በዘፍጥረት 3 ቁጥር 15 ላይ ጌታ አምላክ እባቡን (ሰይጣንን) “በአንተ እና በሴቲቱ (ሔዋን)፣ በዘርህና (זַרְעֲךָ֖) በዘርዋም (זַרְעָ֑הּ) መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፣ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፣ አንተም ሰኮናውን ትቀጠቅጣለህ”  ያለውን ልብ ብለን ብንመለከት እባቡ (ሰይጣን) ዘር እንዳለው የተናገረው ጌታ እግዚአብሔር ራሱ ነው። በእብራይስጡ ዘርህ እና ዘርዋ የሚሉት ቃላት አንድ ዓይነት ዘርን ነው የሚያመለክቱት። እባቡ ማለትም ሰይጣን ዘር እንዳለው ብቻ ሳይሆን ጌታ አምላክ የተናገረው በሴቲቱ ዘር (በክርስቶስ) እና በእባቡ ዘር (ሃሰተኛው ክርስቶስ) መካከል ስለሚኖረው ጦርነትና ስለክርስቶስ የመስቀሉ ድልም ነው። ጌታ ኢየሱስ (ከወንድ ፈቃድ ያልተወለደው፣ በመንፈስ ቅዱስ ከሴቲቱ ዘር የተወለደው) ጠላትን ያሸነፈው በመስቀሉ ሲሆን የእባቡን ዘር ፈጽሞ የሚቀጠቅጠውና ሁሉን ከእግሩ በታች የሚያስገዛው የእባቡ ልጅ የሆነውን ሃሰተኛውን ክርስቶስን፣ ሃሰተኛውን ነቢይና ሰይጣንን ራሱን ወደ እሳት ባህር ሲጥል ነው። ይህ ደግሞ የሚሆነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ዳግመኛ ተመልሶ ሲመጣ ነው።

ስለመላእክት ትክክለኛ መረዳት እንዲኖረን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለነዚህ ሰማያዊ ፍጥረታት የተጻፈውን በጥንቃቄ ማጥናት ያሻል። መላእክት እንግዶች ሆነው መጥተው እግራቸውን ታጥበዋል፣ ምግብ በልተዋል (አብርሃም፣ ማኑሄ) መስዋእት ተቀብለው በእሳት እንዲቃጠል አድርገዋል (ማኑሄ) ፣ በአካል ተገልጸው ከሰው ጋር ታግለዋል (ያእቆብ)፣ በአካል ወደሰው ቤት እንግድነት ገብተው አደጋ ሲፈጠር በር ዘግተዋል (ሎጥ ቤት ሰዶም)፣ የሰዎችን እጅ ይዘው ከጥፋት አድነዋል (ሎጥ)፣ ወዘተ።  ይህ ርዕስ ደግሞ ራሱን የቻለ ትምህርት ይፈልጋልና አንድ ነጥብን ብቻ አቅርቤ ይህንን ትምህርት አጠናቅቃለሁ። በዘፍጥረት 6;2 ላይ “የእግዚአብሔር ልጆች” የሚለው ስም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚያመለክተው  በእግዚአብሔር አምላክ በቀጥታ የተፈጠሩ ሕያዋን ፍጥረታትን ነው። እነዚህ ደግሞ መላእክት፣ አዳምና ሔዋን ናቸው። በአዲስ ኪዳን ላይም በክርስቶስ ኢየሱስ የምናምንን ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ብሎ የሚጠራበት ምክንያት በእምነት በክርስቶስ በኩል እንደገና በእግዚአብሔር ስለተፈጠርን ነው። ከላይ እንዳየነው ይህ በአማርኛ “የእግዚአብሔር ልጆች”  ተብሎ  ከእብራይስጡ የተተረጎመው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስ ውስጥ በተጠቀሰባቸው ቦታዎች ሁሉ የሚያመለክተው መላእክትን፣ አዳምንና ሔዋንን፣ ክርስቶስን እና በክርስቶስ ዳግም የተወለዱትን ነው። በዘፍጥረት 6 ላይ ያለው ትርጉም ግን የወደቁትን መላእክት የሚመለከት ነው።

በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ጌታ እግዚአብሔር እስራኤልንና አህዛብን ለማዳን ያደረገውን ስራ ትልቅነትና የክርስቶስን የመስቀሉን ድል ምስጢር ለመረዳት የምንችለው ሰይጣን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ፣ በመንፈሳዊም ሆነ በአካል የሰውን ዘር ለማጥፋት ያደረገውን እና ዛሬም እያደረገው ያለውን የእብሪት ስራ ስንረዳ ብቻ ነው። የእስራኤል ታሪክ ፣ ትግሎች፣ ውድቀትና መነሳት፣ ከኔፊሊም ታሪክ ጋር የተቆራኘ ነው። የኔፊሊምን ታሪክ ካልተረዳን ብዙውን የእስራኤልን ታሪክ፣ በተለይም ደግሞ ከነዓንን መውረሳቸውን፣ የአካባቢውን ህዝቦች ጣዖታት ማምለካቸውንና በዚያም ምክንያት በጠላቶቻቸው መመታታቸውን፣ እንዲሁም ሌሎች ብዙ የብሉይና የሃዲስ ታሪኮች እና ትምህርቶችን ለመረዳት የምንችለው ሰይጣን በኤድን ገነት፣ በኖህ ዘመን፣ በባቢሎን ግንብ፣  በግብጽ ምድር በፈርዖን ባርነት ስር እስራኤል በነበሩ ጊዜ፣ በባቢሎን ምርኮ፣ በሮማውያን፣ በግሪኮችና በሌሎችም ጠላቶቻቸው በኩል ሊያደርስባቸው የነበረውን የጥፋት ምክንያትና ምንጮቻቸውን ስንረዳ ነው። በዚህ በእኛ ዘመንም እንኳን አይሁድን ለማጥፋት ተነስቶ የነበረው የጀርመኑ ናዚ እንቅስቃሴ ከጥንቱ የኔፊሊም መፈጠር ጋር ጥብቅ ግንኙነት እንደነበረው ብዙ ጥናቶችና መረጃዎች ያሳያሉ።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ከመመለሱ በፊት የአመጽ ሰው ወይም የጥፋት ልጅ የሚባለው ሃሰተኛው
ክርስቶስ እንደሚገለጥ፣ እንደገና የተመሰረተችው እስራኤል፣ ሌሎችም አይሁድና የምድርም ህዝብ ሁሉ እንደሚሰግዱለት መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል። ይህ ጌታችን በመገለጡ የሚሽረውና በአፉም እስትንፋስ የሚያጠፋው ዐመጸኛ ሰው መንፈስ ዛሬ በምድር ላይ በግልጽ እየሰራ ነው። ወደ አደባባይ መውጣት ብቻ ሳይሆን ወደቤተ ክርስቲያንም ገብቶ ብዙ አብያተ ክርስቲያን ነን የሚሉ ከሰዶምና ከገሞራ ባላነሰ ዓመጽ ውስጥ ገብተዋል። እዚህ ጋር ክርስቲያኖች ነን የምንል ሁሉ እንድናስተውል ያስ ጋል። ይህ የዓመጽ ሰው የተባለው ሃሰተኛው ክርስቶስ ሲገለጽ እጅግ ብዙ የሆነው የምድር ህዝብ ሁሉ አሜን ብሎ ነው የሚቀበለው። ብዙ ክርስቲያን ነን የሚሉ፣ ነገር ግን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በግላቸው የማያውቁት ሰዎችም ሁሉ ይከተሉታል። ይህን ሰው ምድር ሁሉ፣ ቤተክርስቲያን ነን የሚሉ ብዙዎችም ጭምር፣ የሌሎች ሃይማኖቶች ተከታዮችና እግዚአብሔር የለም ባዮችም እንደሚቀበሉት በመጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ተጽፏል። የዚህ ነገር ምልቶችም በግልጽ በዘመናችን እየታዩ ነው። በቅርቡ ለምሳሌ ከእስራኤል የሃይማኖት መሪዎች የሚወጡ ዜናዎች መሲሁ (ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሳይሆን እነሱ የሚጠብቁት መሲህ) በቅርብ ጊዜ ራሱን ለእስራኤል ሁሉ ይገልጻል ብለዋል። በዚህ ባለፈው ሳምንትም የእስራኤል ፖሊስ ዋና ኮሚሽነር የሆኑት  Roni Alsheikh መሲሁ በቅርቡ ስለሚመጣና እሱን ለማግኘትም ሰዎች ሲሞክሩ ብዙ መጋፋትና ግርግር ሊፈጠር ስለሚችል ዝግጅቶችን እያደረግን ነው ብለዋል። እነዚህን ዜናዎች ከዜና ምንጩ በእስራኤል ከሚገኘው https://www.breakingisraelnews.com።  ድረ ገጽና ሌሎችም ብዙ ምንጮች ማረጋገጥ ትችላላችሁ።

በምንሰማው ዜና ሁሉ መታወክና መረበሽ የለብንም። ጌታ በምን ቀንና ሰዓት እንደሚመጣ አናውቅም። ነገር ግን ዛሬ ወይም ነገ ቢመጣ በምን ዓይነት ሁኔታ ያገኘን ይሆን? እንንቃ! በመጠንም እንኑር እንጂ አናንቀላፋ። በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ክብሩ የጠራን ደግሞ በጌታ ቀን ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ሆነን እንድንገኝ ሊያደርገን ይችላል። እና ከሰማነውና ከታዘዝን ያደርገዋል።
       አዘጋጅና አቅራቢ ዶ/ር በፈቃዱ ብርሃኑ አድማሱ


የኖኀ ዘመን ፥ ኔፊሊም እነማን ናቸው? ከየት መጡ? ምን አደረጉ? ፍጻሜያቸውስ? ትምሕርት 5

የኖኀ ዘመን ፥ ኔፊሊም እነማን ናቸው? ከየት መጡ? ምን አደረጉ? ፍጻሜያቸውስ?  ትምሕርት 5

ዘፍጥረት ምዕራፍ 6 “በዚያን ወራት ኔፊሊም በምድር ላይ ነበሩ ደግሞም ከዚያ በኋላ የእግዚአብሔር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች ባገቡ ጊዜ ልጆችን ወለዱላቸው እነሱም በዱሮ ዘመን ስማቸው የታወቀ ኃያላን ሆኑ።” የሚለው ቃል እጅግ ብዙ መረጃዎችን የያዘ ክፍል ነው። እነዚህ “ስማቸው የታወቀ ኃያላን ሆኑ” የተባለላቸው ኔፊሊምና ዘሮቻቸው ታላቅነታቸው፣ ታዋቂነታቸውና ኃያልነታቸውና ዛሬ እንደምናስበው አልነበረም። ይህን በተመለከተ የሚከተሉትን ነጥቦች በሚገባ እናስተውል።

1ኛ) ኔፊሊምና ዘሮቻቸው በአካል እጅግ ትልልቅ ነበሩ። ግዙፍነታቸው በሰው ልጆች መካከል አልፎ አልፎ ከምናየውና “ትልቅ” ከምንለው የማይወዳደር ነበር። የብሉይ ኪዳን መጻህፍት ይህንን በቀጥታ ያስተምሩናል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ደግሞ ጥንታዊ የሆኑና በአንዳንዶቹ የጌታ ሃዋርያት መልእክቶች ውስጥ በተዘዋዋሪ ተጠቅሰው ያሉ የጥንት መጻህፍት የነዚህ የኔፊሊምና ዘሮቻቸው ቁመት እስከ ሰላሳ ጫማ (እስከ ዘጠኝ ሜትር) እና በላይ እንደነበር ይናገራሉ። የኔፊሊም ጉዳይ ጌታ ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ዘመን የነበሩ አይሁድና የአካባቢው አገሮች ህዝቦች፣ በተለይም ደግሞ የጌታ ደቀመዛሙርትና አብዛኛው የአይሁድ የሃይማኖት መሪዎች እንዲሁም የዋና ዋናዎቹ የአህዛብ መንግስታት መሪዎች ሁሉ የሚያውቁት ጉዳይ ነበር። ልብ ብለን ካስተዋልን እና ከመረመርን ይህን ነገር ጌታ ኢየሱስ ራሱም ሰይጣንን፣ አጋንንትን እና የጨለማውን መንግስት ኃይል በተመለከተ ባስተማራቸው ብዙ ትምህርቶች ውስጥ በውስጠ ታዋቂነት አንዳንዴም በግልጽ ተናግሮታል። ይህንን ለመረዳት ታዲያ የትምህርቶቹን አውድ፣ ያስተማረበትን ቦታ፣ ተማሪዎቹን እና የትምህርቶቹን ዋነኛ ቁም ነገር መረዳት ያሻል። በዚህ በኛ ዘመን ደግሞ ቁመታቸው እስከ ከ 9 እስከ 15 ጫማ የሆኑ የኔፊሊም ዘሮች አጽሞች በምድር ላይ መኖራቸው ባለፉት ሁለት መቶ ዓመታት በብዙ ጋዜጦችና መጻህፍት እንዲሁም ፊልሞች ተዘግቧል።

መጽሐፍ ቅዱስም  ቁመታቸው እስከ 9 ክንድ (ከአምስት ሜትር በላይ) የነበሩ የኔፊሊም ዘር መኖራቸውን በማስረጃ አስደግፎ ከሚናገርባቸው ስፍራዎች አንዱ የእስራኤል ህዝብ ድል የነሱት የባሳን ንጉስ ዐግ ነበር። ይህ ሰው ርዝመቱ 9 ክንድና ስፋቱ 4 ክንድ (ማለትም 5 ሜትር ከ49 በ 2 ሜትር ከ44) በነበረ የብረት አልጋ ላይ ይተኛ እንደነበር በዘዳግም 3 ቁጥር 11 ላይ ተዘግቧል። የአልጋው ቁመትና ስፋት ብቻ ሳይሆን፣ አልጋው በዚያ ዘመን ከብረት መሰራቱም ብዙ ምስጢሮችን ያስተምረናል። አንደኛ የሰውየው ክብደት እጅግ ብዙ ነበር ማለት ነው። ሁለተኛ ደግሞ ብረት ውድ ስለነበር ብዙው ነገር በነሃስ በሚሰራበት ዘመን በብረት አልጋ ላይ መተኛትም ትልቅ ክብር ነበር።
የኔፊሊም ግዙፍነት የቁመት ጉዳይ ብቻ አልነበረም። ዛሬ ለምሳሌ ቁመቱ 6 ጫማ የሆነና ወፍራም የተባለ አንድ ረጅም ሰው፣ ክብደቱ በአማካይ ቢበዛ ከ200 ኪሎ አይበልጥም። ከአራት ዓመት በፊት በአፍጋኒስታን ተራሮች ዋሻ ውስጥ በአሜሪካ ወታደሮች የተገደለ አንድ ግዙፍ ፍጥረት (የኔፊሊም ቅሪት ተብሎ የሚገመት) ግን ክብደቱ ከ 1100 ፖውንድ በላይ ወይም 500 ኪሎ እንደነበር ተዘግቧል። ልብ እንበል ይህ ፍጥረት ቁመቱ 9 ጫማ ብቻ ነው። የባሳን ንጉስ ዐግ ግን ቁመቱ 9 ክንድ ወይም ከ 18 ጫማ  በላይ ነበር። (አንድ የመጽሃፍ ቅዱስ ጫማ 61 ሳንቲ ሜትር ወይም ከ ሁለት ጫማ በላይ ነው)። ስለዚህ ቢያንስ ቢያንስ ክብደቱ ከ2500 ፓውንድ ወይም 1000 ኪሎ በላይ ይሆናል ማለት ነው።  ዐግ ይኖርባት የነበረችው የጥንቷ የባሳን ከተማ ዛሬ TELL ASHAREH ልትሆን እንደምትችል ተዘግቧል። በዚያች ከተማ ዛሬም ቢሆን በጥንት ዘመን የተሰራ ከፍታው 70 ጫማ የሚሆን የአፈር ክምር (ድልድል) አለ። እንደዚህ ያሉ ድልድሎችን ኔፊሊምና ዘሮቻቸው እንደ መቃብርና እቃዎቻቸውን ለመሸሸጊያ ይጠቀሙበት እንደነበር ሌሎች የታሪክ መረጃዎች ያስረዳሉ።
ኦሪት ዘሆልቁ 13:32 እና 33 ደግሞ አስራ ሁለቱ የእስራኤል ሰላዮች የከነዓን ምድር ከኔፊሊም ወገን በሆኑና ግዙፍ ሰዎች የተሞላ እንደነበር ዘግበዋል። የባሳንን ንጉስ ዐግን ጨምሮ በመጽሐፍ ቅዱስ 22 እጅግ ግዙፍ የሆኑ ሰዎች (የኔፊሊም ዘሮች) ነበሩ የኔፊሊም ዘር የነበራቸው ጎሳዎች ደግሞ ወደ 36 ይደርሳል።

2ኛ) ኔፊሊምና ዘሮቻቸው ይህንን ያህል ግዙፍ ከሆኑ ምን አይነትና ምን ያህል ምግብ እንደሚበሉም መገመት ያስፈልጋል። ያንን የምግብ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የምድርን ተክሎች እና እንስሳትን ያለአገባብ በማዳቀልና በመበከል ተግባሮች ላይ በመሰማራት የእግዚአብሔርን ፍጥረት ማበላሸትና ማጥፋት ይዘው እንደነበር የሚያሳዩ ብዙ ምልክቶች በመጽሐፍ ቅዱስና በሌሎችም የታሪክ መረጃዎች ውስጥ ይገኛሉ። ለምሳሌ አስራ ሁለቱ የእስራኤል ሰላዮች ምድሩን ሰልለው ሲመለሱ ከኤሽኮል ሸለቆ አንድ የወይን ዘለላ ቆርጠው ለናሙና አምጥተው ነበር። ይህ ቆርጠው ይዘው የመጡት የወይን ዘለላ ትልቅ ከመሆኑ የተነሳ በመሎጊያ (ሽመል) ላይ ተደርጎ በሁለት ሰዎች ትከሻ መካከል ተንጠልጥል መምጣት ነበረበት። ማለትም ቢያንስ ይህ አንድ ዘለላ ከ20 እስከ 30 ኪሎ ድረስ ሊህን ይችላል ማለት ነው። ፍጥረታትን ከመበከልም አልፈው እነዚህ ፍጥረታት እጅግ የሚዘገንነው ሰውንና የራሳቸውን ዘር የመብላት ልማድ እንደነበራቸው የሚገልጽ ታሪክ አለ።






ባለፉት ስድሳና ሰባ ዓመታት ከምድር ላይ ረሃብንና በሽታዎችን እናጠፋለን በሚል ሰበብ የሚካሄዱት ተክሎችን፣ እንስሳትንና የሰውንም ዘር ሳይቀር ያለ አገባብ ለመቀየር የሚካሄዱት ስራዎች ምናልባት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመመለሱ በፊት እንደገና ምድር ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ ለማመጽ የመነሳሳቷ ምልክቶች ይሆኑ ?! ከልክ ያለፈ በማዳበሪያ፣ በሆርሞንና በተለያዩ ሰው ሰራሽ መርዛማ ንጥረ ነገሮች የተበከሉ ምግቦች እንዲሁም ደግሞ አዋቂ ነን የሚሉት የዘራቸውን መሰረት የለወጧቸው ተክሎችና እንስሳት (Genetically Modified Organisms ወይም GMOs) በሰው ዘር ህይወትና ጤንነት ላይ እያመጡት ያለው ጣጣ ገና ካሁኑ እጅግ ብዙ ሆኗል። በእኛ ዘመንም እንኳን የምንጠቀምባቸው ድንቅ የተባሉ መርዞች የምድርን ንብ መፍጀታቸውና ይህም ለምድር ሁሉ አስጊ መሆኑ ዜና ከሆነ ውሎ አድሮአል። በሽታን ይከላከላሉ ተብለው በክትባት ውስጥ የሚጨመሩ እንደ ሜርኩሪ ያሉ ከባድ ብረቶች፣ ንጥረ ነገሮችና ቅመሞች እጅግ ብዙ ህዝብን ለካንሰርና ለሌሎችም በሽታ እያጋለጡ መሆናቸውም የአደባባይ ምስጢር ነው።

3ኛ) ኔፊሊም  በአካል ግዙፍ መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ከሰዎች ልጆችም እጅግ የበለጠ እውቀት፣ ኃይልና ቴክኖሎጂም ነበራቸው። ከሰዎች ሴቶች ልጆች የወለዱአቸው አባቶቻቸው የወደቁ መላእክት ስለነበሩ ነፊሊም አማልክት ነን ብለው የሰው ልጆችን እንደባሪያ መግዛት የሚያስችሉአቸውን የተከለከሉ እውቀቶችና ቴክኖሎጂዎችን ሰጥተዋቸው ነበር። ልብ እንበል የነዚያ የኔፊሊምና የአባቶቻቸው ሁሉ ዋነኛ አለቃ ሰይጣን ዓላማ የጌታ የእግዚአብሔርን ቦታ መውሰድ ነበር። ይህ ስለማይሆንለት ደግሞ ጌታ አምላክ በአምሳሉ የፈጠረንን እኛን የሰውን ልጆች ለመግዛትና ለማጥፋት ተነሳሳ።  ይህንን ኃይላቸውንና የላቀ እውቀታቸውን በመጠቀም ከላይ እንዳየነው የሚፈልጉትን ምግብን ለማግኘትና በክፋትም ጭምር የእንስሳትንና የተክሎችን ምንነትና ባህርይ በመቀየር (HYBRIDIZATION and GENETIC ENGINEERING) ተግባር ላይ ተሰማርተው ነበር። በነሱ አስተሳሰብ ተራ የነበረው የሌላው ህዝብ ቁጥር እንዳይበዛ ደግሞ ጽንስን ማስወረድን እና የመገዳደያ መሳሪያዎችን አሰራር ለሰዎች ያስተማሩ እነሱ እንደነበሩ የሚያስረዱ ብዙ መረጃዎች አሉ። ከነሱ ሰውነት ጋር የሚሄዱ እጅግ ታላላቅ ህንጻዎችን፣ መድረኮችን፣ መሰዊያዎችን፣ ፒራሚዶችን፣ ዋሻዎችን እና የዋሻ መንገዶችን ይሰሩ ነበር። ሰውነታቸው እጅግ ትልቅ ስለነበር ትልልቅ ድንጋዮችን መቁረጥና ማንቀሳቀስ ይችሉ ነበር። ዛሬ ካሉን ቴክኖሎጂዎችም የላቀ የምህንድስና፣ የግንባታ፣ የኃይል ምንጭና የማጓጓዣ ቴክኖሎጂ እንደነበራቸው ይታመናል። ለምሳሌ የምድርን የስበት ኃይል የሚቋቋም (ANTI GRAVITY) የማንሳፈፍ ችሎታ እንደነበራቸው ይታመናል። ለዚህ ይሆን ዛሬም በአጋንንት ሥልጣን ተሰጠን የሚሉ ሰዎች እቃዎችን የሚያንሳፍፉት? የሰላቢ መንፈስ የሚባለውስ ከዚህ ጋር የተያያዘ ይሆን? ምናልባት እነዚያ ኔፊሊም እንደገና ወደምድር መምጣት ስለጀመሩ ይሆን በብዙ ሺ ዓመታት እንኳን ያልደረስንበትን ቴክኖሎጂ በድንገትና በፍጥነት ባለፉት ከ100 በማይበልጡ አመታት ያገኘነው?? ምናልባት እነሱ እንደገና ብቅ ብቅ ማለት ስለጀመሩ ይሆን ታላላቆቹ የምድር መንግስታትና ህዝቦች ሁሉ ጨለማውን ብርሃን ብርሃኑን ጨለማ ለማለት ጌታ አምላክን እየተዳፈሩ ያሉት? በሚቀጥሉት ትምህርቶች ላይ ይህንን በበለጠ ዝርዝር እንመለከታለን።

4ኛ) በአፈታሪክ አማልክትና ታላላቅ የጥንት ነገስታት ተብለው እስከዛሬ ድረስ በየትምህርት ቤቱና በየዩ
ኒቨርሲቲው ታሪካቸው እንደትምህርት የሚሰጥላቸው የግሪኮቹ አይሲስና ኦሳይሪስ፣ የባቢሎኖቹ በአል፣ አስታሮትና፣ ታሙዝ፣ የግሪኮቹ አፖሎና አቴና፣ የሮማውያኑ ጁፒተርና ማርስ ወዘተ በሙሉ የኔፊሊም ዘሮች ነበሩ። በታሪክ ሲያስተምሩን ግን ስማቸው ብዙና የሰው የሚመስል የፈጸሙት ጀብዱ ግን ሰው ሊያደርገው የማይችል ነው።  ሊያሳምኑን እንደሚፈልጉት ታዲያ እነዚህ ሁሉ የሰው ሃሳብ የወለዳቸው ተረት ተረት ሳይሆኑ በርግጥም በአካል የነበሩ ፍጥረታት ናቸው። እነዚህን አማልክት ነው ዳዊት በመዝሙር 95(96) ቁጥር 5 ላይ “የአሕዛብ አማልክት አጋንንት ናቸውና እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሰራ።” የሚለው። ይህን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ መረጃ አለው። ለዚህም ነው በየዘመኑ የተነሱ አምባ ገነኖች፣ የሃሰት ሃይማኖት መሪዎች መጽሐፍ ቅዱስን፣ ነቢያትን፣ ሃዋርያትን እና እውነተኛ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት ይጥሩ የነበረው። ነገር ግን ብርሃን በጨለማ ይበራል ጨለማውም አላሸነፈውም።

5ኛ) የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ ፈቃድ በመጣስና የተሰጣቸውን የክብር ስፍራ በመተው ወደ  ምድር በመውረድና ከሰዎች ሴቶች ልጆች ጋር ዘራቸውን ያደባለቁት የወደቁት መላእክት ከመውደቃቸው በፊት ስማቸው “የእግዚአብሔር ልጆች” ወይም በእብራይስጥ “הָֽאֱלֹהִים֙ בְּנֵ֤י”  (ብነይ ሃ ኤሎሂም) ነበር። ከወደቁ በኋላ ግን እነሱም ልጆቻቸውም ኔፊሊም ይባላሉ። በእብራይስጥ ኔፊሊም ማለት “የወደቁት” ማለት ነው። ሐዋርያው ጴጥሮስና ይሁዳ እንደ ጻፉት እነዚያ የወደቁት መላእክት ዛሬ በጨለማ ጉድጓድ ውስጥ እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ታስረዋል። የመጀመሪያዎቹ የወደቁት መላእክትና በኖህ ዘመን ከነሱና ከሰው ልጆች ሴቶች የተወለዱት ልጆቻቸው ደግሞ በጥፋት ውኃ ጠፍተዋል። ከዚያም በኋላ ሌሎች የወደቁ መላእክት ይህንኑ በደል እንደገና እንደፈጸሙ ዘፍጥረት 6  እና ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም ያስተምሩናል። እነዚህ ግዙፍ፣ ኃያላንና እኩያን ፍጥረታት (ኔፊሊምና ዘሮቻቸው) ሙሉ በሙሉ ሰብዓዊ ፍጥረት አይደሉምና ሲሞቱ ነፍሳቸውና መንፈሳቸው ወደ ፈጣሪ (ወደ እግዚአብሔር) መመለስ አይችልም። ስለዚህ በዚሁ በምድር ላይ ይቅበዘበዛሉ። እነዚህ ናቸው አጋንንት የተባሉትና ሁል ጊዜ አካልን ለመልበስ ስለሚናፍቁ ወደ ሰዎች ውስጥ መግባት የሚፈልጉት። በወንጌል ላይ እንደምናነበው፣ ጌታ ከፈቀደላቸው እነዚህ የሞቱት የኔፊሊም መንፈሶች ወደ አሳማዎችም ውስጥ ቢሆን ለመግባት ደስተኞች ናቸው።እንስሶች ግን ሊሸከሙአቸው ስለማይችሉ ወደ  ባህርም ሆነ ወደ እሳት ገብተው ይሞታሉ። ለዚህ ነው አጋንንት ወደሰዎች ሲገቡ ሰዎች የሚታመሙት፣ እጅግ ክፉ የሆነ ነገርን የሚፈጽሙት፣ በተለያየ መንገድም ራሳቸውን ለማጥፋት የሚፈልጉት። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእውነት በርሱ ላይ ለሚያምኑ ሁሉ በነዚህ እኩይ መናፍስት ሁሉ ላይ ሥልጣንን ሰጥቷል። በክርስቶስ በኩል ከእግዚአብሔር ዳግም ለተወለዱና ለሚከተሉት ለደቀ መዛሙርቱ ጌታ ኢየሱስ እንዲህ አለ፤  “እንዲህም አላቸው፣ ሰይጣንን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ። እነሆ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣንን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጎዳችሁም ምንም የለም። ነገር ግን መናፍስት ስለተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ፥ ስማችሁ ግን በሰማያት ስለ ተጻፈ ደስ ይበላችሁ።” ሉቃስ ምዕ 10 ቁ 18፣20። ማንኛውም በዚህ ሰማያዊ ሥልጣን መኖር የሚሻ የክርስቶስ ተከታይ ሁሉ ታላቅ ኃላፊነት አለበት። ኃላፊነቱም የእግዚአብሔርን ቃል ጠንቅቆ መረዳት፣ ለተገለጠለትም የቃሉ እውነትና ለመንፈስ ቅዱስ አመራር ሁሉ በመታዘዝና የእግዚአብሔርን ሥም በሚያከብር አካሄድ መኖር ነው።  


ኔፊሊምን ከሰዎች ሴቶች ልጆች የወለዱት እነዚያ የወደቁት መላእክት እነማን ናቸው፣ መላእክት አካል አላቸው ወይ፣ ይህንንስ ከላይ የተገለጸውንስ ማድረግ ይችላሉ ወይ? የሚሉትን ጥያቄዎች በትምህርት 6 ላይ እንመለከታለን። አዘጋጅና አቅራቢ ዶ/ር በፈቃዱ ብርሃኑ አድማሱ።

በኖኅ ዘመን ምን ሆነ? ትምህርት 4

በኖኅ ዘመን ምን ሆነ?      ትምህርት 4

ይህንን ትምህርት ለመረዳት የቀደሙትን ትምሕርቶች ማንበብ ያስፈልጋል። በትምህርት 3 መጨረሻ ላይ በጣም ባጭሩ እንዳቀረብሁት፣ በግብጽ የሚገኘውን ትልቁን የጊዛ ፒራሚድና ሌሎችንም በምድር ላይ ያሉ እጅግ አስገራሚና ትልልቅ ስራዎች ማን ሰራቸው የሚለው ጥያቄ እስከ ዛሬ ድረስ ሳይንሳዊና ታሪካዊ ወይም በመረጃ የተደገፈ መልስ ያላገኘ ጉዳይ ነው። ታዲያ ማን ሰራቸው የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ታዲያ አንዳንዶች ከሌላ ዓለም የመጡ ፍጥረታት (ALIENS) ወይም የህዋ ተጓዦች የሚለውን ሃሳብ ሲፈጥሩ ሌሎቹ ደግሞ ሊዋጡ የማይችሉ የፈጠራ መልሶችን በማቅረብ እንደኛው ያሉ በድንጋይና በነሃስ መሳሪያ ብቻ ይጠቀሙ የነበሩ ሰዎች ናቸው የሰሩት በማለት ፍንክች አንልም ብለዋልል። እውነቱን ሊረዳ ለሚፈልግ ግን መጽሐፍ ቅዱስ ለዚህ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው የሰው ዘርና ፍጥረት በሙሉ ላለበት ቀውስና መውጫ የሌለው ችግር ሙሉ መልሶች አሉት። እስቲ አሁን ደግሞ ታዲያ ወደዚህ ወደዘለዓለማዊው የእውነት ኢንሳይክሎፒዲያ መለስ እንበልና የሚለውን እንመልከት።

መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር የፈጠራቸውና ህይወት ያላቸው ፍጥረታት መላእክት (ወይም ሰማያዊ፣ መንፈሳዊ ፍጡራን)  የሰው ዘር፣ እንስሳትና እጽዋት ከዚያም ደግሞ ርኩሳን መናፍስት ወይም አጋንንት ብቻ እንደሆኑ ያስተምራል። ታዲያ እነዚህ የዛሬው ዘመን አዋቂና ምሁራን እንዲሁም ተመራማሪዎች ነን የሚሉት ALIENS ብለው የሚጠሩት ከነዚህ ፍጥረቶች የትኞቹን ነው። ከነዚያ ከዋክብት፣ ከነዚያ ፕላኔቶችች፣ ከዚያኛው ጋላክሲ የመጡ ናቸው የሚለው ምናባዊ እውቀት ምንም መረጃ የሌለው የሃሳብ ሩጫ ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስ አጋልጦ አጋንንት፣ የወደቁ መላዕክት፣ ኔፊሊም ያላቸውን በአዲስ የስጦታ ወረቀት ጠቅልሎ የሰው ልጅ እንዲቀበላቸው ለማድረግ የሚደረግ ሙከራ ነው። በርግጥ እነዚህን ALIENS፣ SPACE TRAVELLERS, EXTRA TERRESTRIAL INTELLIGENCE የሚባሉትን ነገሮች እውነተኛ ምስጢር ሁሉም ሳይንቲስት፣ ተመራማሪ ወይም ጋዜጠኛ እና የታሪክ አዋቂ ነኝ ባዩ ሁሉ ያውቃል ማለት አይደለም። እንደሌሎቹም ብዙ የእውቀት መስኮች ሁሉ አውቀው የተደበቁ መሪዎችና ሳያውቁ ተታልለው የሚከተሉ ጀሌዎችም አሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ግን እነዚህ እነሱ በተለያየ ዘመናዊና ሳይንስ መሰል ስሞች የሚጠሯቸው ማን መሆናቸውን በብዙ ማስረጃና በግልጽ ያስረዳል። በዘፍጥረት ምዕራፍ 6 ቁጥር 1 እስከ 4 ድረስ እንዲህ ይላል፤

“እንዲህም ሆነ ሰዎች በምድር ላይ መብዛት በጀመሩ ጊዜ ሴቶች ልጆች ተወለዱላቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆችም የሰውን ሲቶች ልጆች መልካሞች እንደሆኑ አዩ፣ ከመረጡአቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ። እግዚአብሔርም፥ መንፈሴ በሰው ላይ ለዘላለም አይኖርም እርሱ ሥጋ  ነውና፥ ዘመኖቹም መቶ ሀያ ዓመት ይሆናሉ አለ። በእነዚያ ወራት ኔፊሊም በምድር ላይ ነበሩ ደግሞም ከዚያ በኋላ የእግዚአብሔር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች ባገቡ ጊዜ ልጆችን ወለዱላቸው እነርሱም በዱሮ ዘመን ስማቸው የታወቀ ኃያላን (በእብራይስጡ הַגִּבֹּרִ֛ים ሀጊቦሪም፣ ወይም እጅግ ግዙፍና ኃያላን የሆኑ ፍጥረታት) ሆኑ።” ዘፍጥረት 6፤1

በዚሁ በምዕራፍ 6 ቁጥር 7 ላይ እግዚአብሔር አምላክ በምድር ላይ በነበረው ክፋትና ዓመጽ እጅግ እንደ ተቆጣ፣ ሰውንም በመፍጠሩ እንደ ተጸጸተና የፈጠረውንም ሰውና እንስሳ ሊያጠፋ እንደወሰነ ይናገራል። ምክንያቱም እነዚያ “የእግዚአብሔር ልጆች” የተባሉት የሰውን ልጆች ሚስቶች አድርገው ስለወሰዱ፣ ከዚህም ያልተፈቀደ ግንኙነት ውስጥ ኔፊሊም የሚባሉት ግዙፍ የሆኑ ፍጥረታት ስለተወለዱ እና ኔፊሊም፣ ዘሮቻቸውና የተባበሩአቸው የምድር ሰዎችም ምድርን በዓመጽ ስለሞሏት ነበር።  እነዚያ “የእግዚአብሔር ልጆች” የተባሉት ማን እንደሆኑ፣ ለምን ከነሱና ከሰዎች ሴቶች ልጆች የተወለዱት ግዙፎችና ኃያላን እንደሆኑና የነሱንም ታሪክና ፍጻሜ በሚቀጥለው ትምህርት ላይ እንመለከታለን።  ለአሁኑ ግን ጌታ እግዚአብሔር ምድርን በሙሉ በውኃ ያጠፋበት ምክንያት ላይ እናተኩር። ይኽው ዘፍጥረት 6 ምክንያቱን ሲዘረዝር እንዲህ ይላል፤ 1ኛ) የሰው ክፋት በምድር ላይ በዛ 2) የሰው የልቡ ሃሳብና ምኞት ሁል ጊዜ ፈጽሞ ክፉ ሆነ 3) ምድር (ሰዎች፣ እንስሳት፣ ተክሎች፣ መሬቱና ሌሎችም ግኡዛን ፍጥረታት) ተበላሸች 4)ምድር ግፍን ተሞላች 5) ስጋን የለበሰ ሁሉ መንገዱን አበላሽቶ ነበር። እነዚህ ኃጢዓቶች ከጥፋት ውኃ በፊትና ዛሬም በሰው ልጆች ከሚፈጸሙት በደሎች ሁሉ በዓይነትና በመጠንም እጅግ የከፉና በዘመኑ የነበረውን የሰውን ዘር ሁሉ ያካተቱ እንጂ በአንድ ወይም በጥቂት አካባቢዎች ብቻ በተወሰኑ ሰዎች የተፈጸሙ አልነበሩም።  

መጽሐፍ ቅዱስ የጥፋት ውኃ ሆነ ባለበት ዘመን (በግምት በ 2348 ዓመተ ዓለም) አካባቢ በምድር ሁሉ ላይ በውሃ ጠፍተውና በደለል ተሸፍነው የነበሩ ቦታዎች፣ በኔፊሊም የተሰሩ ግዙፍ ስራዎችና አጽሞችም ሳይቀር በዝቅተኛ፣ በተራራማና በከፍተኛ ቦታዎችም (plateaus) ላይ ሳይቀር ተገኝተዋል፣ እየተገኙም ነው። ባጭሩ ለማስቀመጥ ኔፊሊምና ህገ ወጥ አባቶቻቸው (የወደቁት መላዕክት) ነበሩ ለሰው ልጅ የጦርነትና የመገዳደልን መሳሪያዎችና ተንኮልን፣ ህገወጥና ከተፈጥሮ ባህርይ ውጭ የሆነ  ፍትወተ ሥጋን፣ ልቅ የሆነ ዓለማዊነትንና ዘማዊነትን፣ ገደብ የለሽ የገንዘብ፣ የስልጣንና የዝና ስግብግብነትን እና ሌሎች እስከዛሬ ድረስ የሰው ልጅን እየፈጁና እያፋጁ ያሉ ክፋቶችን ያስተማሩት። የወንድና የሴት ሰዶማዊነትን፣ በሰውና በእንስሳት መካከል የሚደረግ ርኩስ ፍትወተ ስጋን እና ለመናገርም እንኳን የሚዘገንኑ ሌሎች ርኩሰቶችን ያስተማሩ እነዚህ ኔፊሊም የተባሉ እኩይ ፍጥረታትና ዘሮቻቸው ነበሩ። በማህጸን ውስጥ ጽንስን መግደልን፣ የሰውንና የእንስሳን ዘር በማደባለቅ አስፈሪ፣ አደገኛና ዘግናኝ የሆኑ ፍጥረታትን ማስወለድ፣ ሰዎች ከአምላክ ይልቅ እነሱን ራሳቸውን (ኔፊሊምንና ዘሮቻቸውን)  እንዲያመልኩ ማድረግ፣ ህጻናት ልጆቻቸውንና  ትልልቆችንም ሰዎች ለነሱ (ለኔፊሊም ገዥዎቹ) መስዋእት እንዲሰውላቸው ማድረግን ያስተማሩ እነዚሁ የወደቁት መላእክትና ልጆቻቸው ናቸው። ከዚህም አልፈው ከሰውና ከእንስሳት እንዲሁም ከራሳቸው ከኔፊሊምና ከተለያዩ እንስሳት ዘር የተደባለቁ ግማሽ ሰውና ግማሽ እንስሳ ፍጥረታት እንዲፈጠሩ በማድረግ የእግዚአብሔርን የተፈጥሮ ስርዓት በሙሉ ሊያጠፉት ተቃርበው ነበር። ከኖህና ከቤተሰቡ ከእርሱም ጋር ወደመርከብ ከገቡት እንስሳት በስተቀር የቀሩቱ የምድር ፍጥረት በሙሉ በኔፊሊም ዘርና በነሱም የረከሰ የኑሮ ዘይቤ የተበከሉና የዓመጻውም ተካፋዮች ነበሩ። ሐዋርያው ጴጥሮስ የኖህን ዘመን የወደቁ መላእክት አመጽና ውጤቱን እንዲህ ሲል ገልጾታል:

“እግዚአብሔር ኃጢዓትን ላደረጉ መላዕክት ሳይራራላቸው ወደ ገሃነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ቀን ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው፣ ለቀደመውም ዓለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ጽድቅን የሚሰብከውን ኖኅን አድኖ በኃጢዓተኞች ዓለም ላይ የጥፋትን ውኃ ካወረደ>>>” 2ኛ ጴጥሮስ 2፤4 እስከ 5

የይሁዳ መልእክት ደግሞ የወደቁት መላእክት፣ የልጆቻቸው የኔፊሊም እና የተባበራቸውም የኖህ ዘመን ዓለም የሰሩትን ታላቅ ኃጢዓት እንደሚከተለው ገልጾታል፤

“መኖሪያቸውንም የተውትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርስ ድረስ ጠብቆአቸዋል። እንዲሁም እንደ እነርሱ ዝሙትን ያደረጉና ሌላን ሥጋ የተከተሉ ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸውም የነበሩ ከተማዎች በዘላለም እሳት እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል።” ይሁዳ ቁጥር 7 እና 8።

ይህንን ክፍል ስናነብ ቢያንስ የሚከተሉትን ነጥቦች እናስተውል። በኖህ ዘመን የወደቁት መላእክት ሌላ ሥጋን (የሰውን ሴቶች ልጆችን) ተከትለው የተከለከለ ግብረ ስጋ ግንኙነትን ፈጽመው ነበር። ሰዶምና ገሞራም የጠፉበት ኃጢዓትም እንዲሁ በሰዎች ወንዶችና ወንዶች ወይም በሶዎች ሴቶችና ሴቶች መካከል የተፈጸመ ዝሙት ብቻ ሳይሆን በወደቁ መላእክት፣ በዘሮቻቸው በኔፊሊምና በሰዎች እንዲሁም በእንስሳት መካከል የተደረጉ እጅግ ክፉ ዓመጻዎችም ነበሩ ማለት ነው።


ዘፍጥረት 6 “የእግዚአብሔር ልጆች” የሚላቸው እነማንን ነው? መላእክት እንደሰው ሰውነት አላቸው ወይ? ኔፊሊም ለምን ግዙፍና ኃይለኛ ሆኑ? ኃይለኛ ማለት ምን ማለት ነው? ዛሬ በዓለማችን አስደናቂ ከሚባሉ የጥንት ስራዎች ጋር ኔፊሊም ግንኙነት አላቸው ወይ? የሚሉትን ጥያቄዎች በሚቀጥለው ትምህርት 5 ላይ እንመለከታለን።   አዘጋጅና አቅራቢ ዶ/ር በፈቃዱ ብርሃኑ አድማሱ

የኖህ ዘመን እንደነበረ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት እንዲሁ ይሆናል፥ ትምህርት ቁጥር 3

የኖህ ዘመን እንደነበረ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት እንዲሁ ይሆናል፥   ትምህርት ቁጥር 3
በትምህርት 1 እና 2 ላይ እንደተመለከትነው እጅግ አስደናቂ የሆኑና እንደ ብርቅ የሚታዩ ብዙ ጥንታዊ ስፍራዎች አሉ፣ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ቱሪስቶች ይጎበኛሉ፣ በተለያየ የእውቀት መስክ በተሰማሩ ተማራማሪዎችና ምሁራንም እየተጠኑ ናቸው። ለምሳሌም ያህል የጠቀስኳቸው የግብጽ ፒራሚዶች፣ በሊባኖስ ባዓልኤክ የሚገኘው የጁፒተር ቤተ መቅደስ፣ በካምቦዲያ የሚገኘው የአንግ ኮር ዋት ቤተ መቅደስ እንዲሁም በሜክሲኮ፣ በፔሩ እና በሌሎችም የደቡብ አሜሪካ አገሮች፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በእስያ የሚገኙ እጅግ ብዙ ፒራሚዶች፣ ቤተ መቅደሶች፣ ታላላቅ የጥንት የአምልኮና የስፖርት ማእከሎች፣ አገርን ከአገር እና ከተማን ከከተማ የሚያገናኙ የመሬት ውስጥ ዋሻዎችና መንገዶች እንዲሁም ባህር የከደናቸው ከተሞች አሉ። ከአንደኛ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ የተማርናቸው የታሪክ፣ የአርኮዎሎጂ እና ሌሎችም የህብረተሰብ ሳይንሶች እንደ ነገሩን ከሆነ ታዲያ እነዚህ ግዙፍ፣ አስደናቂና ውስብስብ ነገሮች የተሰሩት የሰው ልጅ የድንጋይ መሳሪያዎችን ከመጠቀም አልፎ የነሃስ መሳሪያዎችን መስራት በጀመረባቸው ዘመናት ነበር። ታዲያ የሰው ልጅ ብረትንና የብረትን መሳሪያዎች እንኳን ገና ባልሰራበት በዚያ ዘመን እንዴት አድርጎ ነው እነዚህን እጅግ ታላላቅ ነገሮች የሰራው የሚለውን ጥያቄ ተመራማሪዎች እስከ ዛሬ ሊመልሱት አልቻሉም። እነዚህ ግዙፍ ስራዎች እንኳን በነሃሱ ዘመን ይቅርና ዛሬ በ21ኛው ክፍለ ዘመንም እንኳን የሰው ልጅ በደረሰበት የእውቀትና የቴክኖሎጂ አቅም ለመሰራት እጅግ አዳጋች፣ ብዙ ጊዜና ወጭ የሚጠይቁ ናቸው። ለምሳሌና የነዚያን የጥንት ስራዎች ከባድነት ለማነጻጸር ያህል ባለፈው በ2016 ዓም በዘመናዊቷ በስዊትዘርላንድ ውስጥ ተጠናቆ የተመረቀው የጎታርድ የምድር ውስጥ መንገድ (TUNNEL) ለምሳሌ ቁመቱ 15 ኪሎ ሜትር ሲሆን በመጀመሪያ ስራው የተጀመረው በ1871 ዓም ነበር። በጊዜው በብዙ ችግሮች ምክንያት ሊጠናቀቅ ስላልቻለ እንደገና በ1990ዎቹ መጨረሻ ላይ ተጀምሮ ከ18 ዓመታትና ከ23 ቢሊዮን ዶላር ወጭ በኋላ ነበር በ2016 ስራው የተጠናቀቀው።
እስቲ ለምሳሌ ያህል ከነዚህ ትልልቅ የጥንት ዘመን ስራዎች መካከል አንዱን ብቻ ባጭሩ እንመልከት። ከአባይ ወንዝ በስተምዕራብ ድሮ ሜምፊስ ተብላ ትጠራ ከነበረችው ከተማ ሳይርቅና በዛሬዋ የካይሮ ከተማ ፊት ለፊት የሚገኘው እጅግ ታላቅ የሆነው የጊዛ ፒራሚድ በጣም ከሚታወቁት ታላላቅ የጥንት ስራዎች አንዱ ነው። የዚህ ፒራሚድ አሰራር ፣ ግዙፍነቱ፣ የተሰራባቸው ድንጋዮች ትልልቅነት፣ ከባድነት፣ ጠንካራነት፣ እንከን የሌለው አቆራረጥና ልሙጥ መሆን፣ ፒራሚዱ የተሰራበት ስፍራ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ እና ከታዋቂ የሰማይ ከዋክብትና የከዋክብት ክምችት ጋር ያለው ቅኝት በሙሉ ሲታሰብ ሰሪዎቹ  እጅግ የላቀ የሂሳብ፣ የምህንድስና፣ የጂኦግራፊ፣ የጂኦሎጂ እና የከዋክብት ጥናት እውቀት ብቻ ሳይሆን ዛሬም እንኳን የሰው ልጅ የሌሉት የምህንድስና ቴክኖሎጂ፣ የኃይል ምንጭና የመጓጓዣ መሳሪያዎችም እንደነበሯቸው ያሳያሉ። ብዙ ምሁራንንና ተመራማሪዎችን እዚህ ድምዳሚ ላይ ካደረሱአቸው መረጃዎች አንዳንዶቹ የሚከተሉት ናቸው። የጊዛው ፒራሚድ የተሰራው እጅግ ጠንካራ ከሆነው ግራናይት ከሚባለው ድንጋይና ከኖራ ድንጋይ ነው። በተሰራበት ዘመን የውጭ አካሉ ፍጹም ልሙጥና ለስላሳ ሆኖ ከሰማይ ሲታይ የሚያንጸባርቅ እንደነበር ይታመናል። አንዳንድ አፈ ታሪኮች ደግሞ ፒራሚዱ ቁመቱ ከዘጠኝ ሜትር በላይ (30 ጫማ) ከሆነ ከወርቅ የተሰራ ጫፍ ወይም ቆብ ነበረው ይላሉ።
 ፒራሚዱ ለማያውቀው ተራ የድንጋይ ክምር ይምሰል እንጂ በውስጡ ለመተላለፊያና አየርን ለማንሸራሸር የሚሆኑ ታላላቅ መንገዶች ወይም ኮሪደሮች አሉት። ለማምለኪያ ወይም መስዋእት ማቅረቢያ የተሰሩ የሚመስሉ ክፍሎችም በውስጡ አሉ። ፒራሚዱ የተቀመጠው 57200 ካሬ ሜትር በሚሆን ቦታ ላይ ሲሆን የተሰራው ደግሞ በግምት 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ከሚሆኑ ድንጋዮች ነው። የተሰራባቸውም እያንዳንዱ የግራናይት ድንጋዮች ክብደታቸው እስከ 50 ቶን (50 ሺ ኪሎ) የሚመዝኑ ሲሆን፣ ብዙዎቹ ድንጋዮችም እስከ 100 ቶን (100ሺ ኪሎ) ይደርሳሉ። ፒራሚዱ መሬት ላይ ያረፈበት ቅርጹ አራት ማእዘን (SQUARE) ሲሆን አራቱ ገጾቹ ደግሞ እኩል ቁመት ያላቸው ሶስት ማእዘኖች ናቸው። እነዚህም አራት ገጾች ፊታቸው ወደ ምስራቅ፣ ምእራብ፣ ሰሜንና ደቡብ ያመለክታል። በመጽሐፍ ቅዱስ ክንድ (CUBIT) ሲለካ የእያንዳንዱ የአራቱ ማእዘን ቁመት 365.2422 ክንድ ነው። ይህ ቁጥር ደግሞ በአንድ የጸሃይ ዓመት ውስጥ ያሉትን የፍጹም ቀኖች ቁጥር ያመለክታል። አራቱ ባለ ሶስት ማእዘን ገጾቹ ዘንበል ያሉበት ማእዘን (ANGLE) አራቱ ገጾቹ በ232.52 ክንድ ከፍታ ላይ እንዲገናኙ ያደርጋቸዋል። የፒራሚዱ እግር ያረፈባቸው ሁለት ወገኖች ቁመት ተደምሮ በዚህ ቁጥር (በ 232.52 ሜትር) ቢካፈል በሂሳቡ ዓለም በጣም የሚታወቀውን ቁጥር 3.14159ን ወይም ፓይ (PI) የሚባለውን ይሰጠናል። በመሬት ላይ ያረፈበት የአራቱ ማዕዘኖች ቁመት ሲደመር ደግሞ (365.2422 X 4)=14609.68 ነው። ይህ ደግሞ የፒራሚዱ ቁመት ሁለት እጥፍ የሆነ የወገብ ስፋት ካለው (232.52) ክብ ቅርጽ የዙሪያ ቁመት (CIRCUMFERENCE) ጋር እኩል ነው። ማለትም (232.52 X 2 X 3 3.14159)። ይህ ማለት ደግሞ ፒራሚዱን የሰሩት አራት ማዕዘንን ወደ ክብ መቀየር የሚለውንና ከላይ የተገለጹትንም ውስብስብ የሂሳብ ህጎችና ስሌቶች ማወቅ ብቻ ሳይሆን ሃሳቡንም ይህን በሚያህል ግዙፍ ስራ ላይ ማዋል የሚችሉ ነበሩ ማለት ነው።
ከላይ የተሰጠውን መረጃ እንኳን ረጋ ብለን ብናጠናው እጅግ ብዙ ጥያቄዎችን እናነሳለን። ለመሆኑ እንዴት ነበር ሰሪዎቹ 100 ሺ ኪሎ የሚከብዱ የግራናይት ድንጋዮችን ስህተትና እንከን በሌለው ቅርጽና ፍጹምነት የቆረጡት። ድንጋዩ ከተቆረጠበት ቦታ ፒራሚዱ ወደተሰራበት ቦታ ያጓጓዙት እንዴትና በምን ነበር? ከዚያስ ደግሞ በምንና እንዴት ነበር ድንጋዮቹን እያነሱ ይህንን ተራራ የሚያህል ነገር የገነቡት? እነዚህ እጅግ ግዙፍ የሆኑ ድንጋዮች የተቆረጡበት መሳሪያ ምን እንደነበር እንኳን ሊታወቅ እስከማይችል ድረስ ማእዘናቸው ያለ እንከን የሆነና  ድንጋዮቹም ሲቆረጡ በላያቸው የቀረ የየመጋዝ ወይም የመሮ ምልክት እንኳን የሌለባቸው ለስላሳ ናቸው። ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?
ፒራሚዱ ሌሎች እጅግ ብዙ አስገራሚ ምስጢሮችንም ይዟል። ለምሳሌ ወደላይ የቆሙት የአራቱ ማእዘኖቹ ዝንባሌ (ANGLE) ከቁመቱ ጋር ሲነጻጸር 10 በ 9  ነው። ማለትም ፒራሚዱን እንደመሰላል አድርገን ወደ ላይ አስር ጫማ ብንወጣ ከምድር ከፍ የምንለው ግን 9 ጫማ ብቻ ነው። ይህ ስሌት ምስጢርን ይዟል። የፒራሚዱ ጠቅላላ ከፍታ (232 52 ክንድ) ሲባዛ በ10 ሲባዛ በ9 ኃይል (ማለትም 232 52 X 10^9) የሚሰጠን ቁጥር 91,840,000 ማይል ወይም ከምድር እስከ ጸሃይ ድረስ ያለውን ርቀት ነው። የሰው ልጅ በእጅ የሚገፋ ጋሪ እንኳን ባልነበረው በዚያ ዘመን እነዚያ ገንቢዎች ከምድር እስከ ጸሃይ ድረስ ያለውን ርቀት ማወቅ ብቻ ሳይሆን ማወቃቸውንም ደግም በፒራሚዱ ልኪት ላይ በምስጢር ስሌት ማስቀመጣቸው የዘመናችንን ትልልቅ መሃንዲሶች፣ የሂሳብ፣ የህዋ ምርምርና ሌሎች ሊቃውንትንም ግራ ያጋባ ነገር ነው።

ፒራሚዱ በምድር ላይ የተቀመጠበት ቦታ በካርታ ላይ አሉ ብለን በምንጠቀምባቸው ሃሳባዊ የአግድም እና የቁልቁል መስመሮች (LONGITUDE AND LATTITUDE) ላይ ሲታይ በ30ኛው ዲግሪ ላቲቲውድ እና በ30ኛው ዲግሪ ሎንግቲውድ መገናኛ ላይ ነው የተተከለው። ይህ ቦታ ደግሞ በዓለማችን ላይ ያለውን የብስ አራት እኩል ቦታ የሚከፍል ቦታ ነው። የፒራሚዱ ሰሜናዊ ገጽም ከውነተኛው የምድር ሰሜን ዋልታ ጋር በትክክል የተቀመጠ ነው። ኮምፓስና ማግኔት ባልነበረበት ዘመን ይህን ማድረግ ለሰው ልጅ በፍጹም የማይቻል ነገር ነው ቢባል መረዳቱ ያላቸው ብዙ ሰዎች ይስማማሉ። የምድርን ካርታ በሎንግቲውድ እና በላቲቲውድ ከፍሎ የማስቀመጥ ሃሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ በስራ ላይ የተሞከረው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ2ኛው ዓመተ ዓለም (ከ200 እስከ 101 ዓመተ ዓለም) በግሪካዊው ሂፓርከስ ነበር። ይህ የጊዛ ፒራሚድ ደግሞ ተሰርቶ የተጠናቀቀው በ2560 ዓመተ ዓለም ከክርስቶስ ልደት በፊት፣ ማለትም ሎንግቲውድ እና ላቲቲውድ የሚባሉት መስመሮች ከመታሰባቸው ከ2360 ዓመት በፊት ነበር ማለት ነው።  
የፒራሚዱ ሰሪዎች ፒራሚዱ በምድር ላይ የተቀመጠበትን ቦታ ብቻ ሳይሆን ፒራሚዱ ከሰማይ ከዋክብትና፣ ከዋክብቱም የምድር አራቱ ወቅቶች በተለዋወጡ ቁጥር ሊታዩ የሚችሉበትን አቅጣጫ እና ከፒራሚዱ መስኮቶች ወደ ከዋክብቱ ሊኖር የሚገባውን ዝንባሌም (ANGLE) በትክክል በማስላት  በማነጻጸር ነው  የሰሩት። በፒራሚዱ ሰሜናዊና ደቡባዊ ገጾች (ግድግዳ) ላይ ከውጭ ወደ ፒራሚዱ መሰረት የሚወርዱ ሁለት ሁለት የመተላለፊያ ዋሻ መሰል ቀዳዳዎችን ሰርተዋል። በሰሜን በኩል ካሉት ሁለት ቀዳዳዎች አንዱ ቤታ  ኡርሳ ሌላው ደግሞ አልፋ ድራኮኒስ ወደሚባሉ በድራኮ የከዋክብት ክምችት ውስጥ ወዳሉ የታወቁ ከዋክብት በቀጥታ ያመለክታሉ። በደቡባዊው ገጹ ላይ ያሉት ሁለት ቀዳዳዎች ደግሞ ሲሪየስ እና ዜታ ኦሪዮኒስ ወደሚባሉት ግብጻውያን ያመልኳቸው ወደነበሩ ከዋክብት ያመለክታሉ። ይህ ፒራሚዱ ከሰማይ ከዋክብት ጋር በመገናዘብ የተሰራበት እውቀት በዓለም ላይ ባሉት በሌሎቹም ብዙዎች ጥንታዊ ቦታዎች ስራ ላይ መዋሉ ተረጋግጦአል። ከላይ ባጭሩ የተገለጹትንና ሌሎችንም ብዙ መረጃዎች ያጠኑ ምሁራን፣ ይህ ፒራሚድና ሌሎችም ብዙዎች በምድር ሁሉ ያሉና አስደናቂ የተባሉ የጥንት ስራዎች እንዴት እንደተሰሩና ማን እንደሰራቸው ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ እስከዛሬም ድረስ  ሊያረጋግጡ አልቻሉም። ነገር ግን ታሪካቸው በየትምህርት ቤቱና በየዩኒቨርሲቲው ከሚሰጡት ትምህርቶች ጋር እንዳይጋጭ በማለት ብቻ፣ እነዚህ የጥንት ስራዎች ያሉባቸው አገሮች “የጥንት ህዝቦች ስራዎች” ናቸው በሚል መሸፈኛ ብቻ ያልፉታል።
እግዚአብሔር ግን ራሱንና ቃሉን ያለ ምስክር አይተውምና ባለፉት 200 በሚሆኑ አመታት መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምራቸውን ነገሮች በጥሞናና በብዙ ሳይንሳዊ መንገዶች የሚያጠኑና ቃሉን የሚያምኑ ምሁራን ስለ ግብጹ ፒራሚድም ሆነ ስለ ሌሎቹ አስገራሚ የጥንት ስራዎች አመጣጥ መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጣቸው ብዙ መረጃዎች እንዳሉ ደርሰውበታል። ምድር በጥፋት ውኃ ከመጥፋቷ በፊት ቀደም ብሎና ከዚያም በኋላ በአንድ የተሳሳተ ኪሩብ (ሰይጣን በምንለው) መሪነት ከክብራቸው ከወደቁት እጅግ ብዙ የሰማይ ሰራዊት መካከል አንዳንዶቹ ወደ ምድር በመውረድና የእግዚአብሔርን የፍጥረት ህግ በመጣስ ከሰው ሴቶች ልጆች ጋር በመደባለቅ ኔፊሊም የሚባሉትን እንደወለዱ በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 6 ላይ እናነባለን። እነዚህ ኔፊሊም ደግሞ በምድር ላይ ኃያላን እንደነበሩ በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ እናነባለን። ይህንን መረጃ በሚገባ ተረድተን  እንኳን ሳናበቃ ነው በዚሁ በዘፍጥረት ምእራፍ 6 ላይ ጌታ አምላክ በሰው ልጅ ላይ መቆጣቱንና ምድርን በውኃ ለማጥፋት መወሰኑን ለኖኅ የገለጸው። ከላይ ያነበብነውን የግብጹን ፒራሚድና የሌሎችንም የጥንት ስራዎች በተመለከተ ዘፍጥረት 6 ብቻውን መልሱን በሙሉ አይነግረንም። መነሻው ግን የዚሁ የወደቁት መላእክት ዘራቸውን ከሰው ዘር ጋር የማደባለቁና እጅግ ግዙፍ፣ ኃያላንና ብዙ እውቀትና ቴክኖሎጂ የነበራቸው የኔፊሊም በምድር ላይ መብዛት ነበር።
አማልክት ነን በማለትና የሰውን ልጆች በማስጨነቅ በጥንት ዘመን በምድር ሁሉ ይገዙ የበሩት እነዚህ ኔፊሊምና ከነሱ የወጡ ዘሮች ናቸው። በጥንት ዘመን የታወቁ ኃያላንነበሩ ብሎ ዘፍጥረት 6 የሚጠቅሳቸው እነዚህ እኩይ ፍጥረቶች በኖኅ ዘመን ምድርን በዓመጻና፣ በደም መፋሰስ ምልተዋት ነበር። እነዚህ ናቸው የከነዓንን ምድር ሞልተው ምድሪቱን ያረከሱትና ጌታ አምላክም ሙሴንና እስራኤልን ፈጽማችሁ አጥፉአቸው ብሎ ያዘዛቸው። እነዚህ ናቸው ለሰው ልጅ መፋጀትን፣ ልጆቻቸውን እንደ መስዋእት ለአጋንንት ማቅረብንና ሌሎችንም እጅግ ዘግናኝ ኃጢአቶችን ያስተማሩት። ይህ እውነት ከዘፍጥረት ጀምሮ እስከ ራዕይ ድረስ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተገልጧል። ኔፊሊም እጅግ ግዙፍ ነበሩ። መጽሐፍ ቅዱስም እነዚህን ህቦች ኔፊሊም፣ ራፋይም፣ አናቃውያን፣ ሖራውያን  ኤሚማውያን፣ ዘምዙማውያን፣ ወዘተ በማለት ይጠራቸዋል። እነዚህ ኔፊሊምና ዘሮቻው ናቸው አማልክት ነን በማለት በብዙ ስሞች እስከ ዛሬ ድረስ የሚመለኩት። እነዚህን ህዝቦች ነው ከኢያሱ ጋር ሄደው የነበሩት ሰላዮች “እኛ በፊታቸው እንደ አንበጣ ነን” ብለው የፈሩት።
እነዚያ የኔፊሊም ህገ ወጥ አባቶች የሆኑት የወደቁ መላእክት መበከልና ማጥፋት የጀመሩት የሰውን ዘር ብቻ ሳይሆን እንስሳትንም ነበር። ስለዚህም ዘራቸውን ከእንስሳት፣ የሰውንም ዘር ከእንስሳት ጋር በማደባለቅ ካይሜራ (CHIMERA) የሚባሉ ከፊል እንስሳ ከፊል ሰው የሆኑ አስፈሪ ፍጥረታትን መፍጠር ብቻ ሳይሆን እነዚያ ፍጥረታት እንደ አማልክት እንዲመለኩም ያደርጉ ነበር። ለዚህ ነው የግብጽ አማልክት የሰውና የአንበሳ ድብልቅ (SPHINX)፣ የሰውና የአሞራ ድብልቅ (ለምሳሌ የግብጽ አምላክ ሶካር) እና ሌሎችንም ፍጥረታት በመከላለስ የፈጠሩት። እነዚህ ፍጥረታት በየትምህርት ቤቱ እንደተነገረን ተረት ተረት የፈጠራቸው የሰው ሃሳቦች (MYTH) ሳይሆኑ በእርግጥ የነበሩ ለመሆናቸው ለዘመናት ተደብቀው የነበሩ ብዙ መረጃዎች ወጥተዋል ዛሬም እየወጡ ነው። ዛሬ በኛ ዘመን ደግሞ እነዚሁኑ እኩያን ፍጥረታት ነው በፊልም፣ በልብ ወለድ መጻህፍት፣ በልጆች መጫወቻዎችና በዜና መልክም ሳይቀር ALIENS፣ EXTRA TERRESTRIALS፣ SKY TRAVELLERS ወዘተ በማለት ሊያቀርቡልን የሚሞክሩት። ሰይጣን መላእክቱን በዚህ መንገድ ያሰማራበት ምክንያት ደግሞ የሰውንና የእንስሳትን ዘር በክሎ ለማጥፋት ነበር። ለዚህ ነው ጌታ አምላክ ኖህንና ቤተሰቡንና፣ የተመረጡ እንስሳትን ብቻ በማስቀረት በዚያ ዘመን የነበረውን ዓለም በውኃ ያጠፋው።

የዚህ ዓለም ገዢ ሰይጣንና በሰማያዊ ስፍራ ያሉ የክፋት መንፈሳውያን ሰራዊት መኖራቸውን ብዙዎቻችን ክርስቲያኖች በጨረፍታም ቢሆን ብናውቅም፣ ከዚህ በላይ ባጭሩ ለማቅረብ የሞከርኩትን መረጃ ለማመን ለብዙዎቻችን ከባድ መሆኑን እረዳለሁ። ይህንን መረጃ ያቀረብኩበት ዋነኛ ምክንያ አንድ ነው። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን፣ በዚህ በኛ ዘመንና የሱ ዳግም ምጽዓት በሚቃረብበት  ጊዜ እንደ ኖህ ዘመን ሁሉ የሰይጣን  አሰራር በረቀቀ መንገድ እየተገለጠ ስለሚሄድ ነው። ልብ ብላችሁ ከሰማችሁና ካያችሁ ብዙ ፊልሞች፣  መጻህፍት፣ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች፣ የህጻናት ፊልሞችንም ጨምሮ የሚያወሩትና የሚያሳዩት ስለ ALIENS፣ EXRA TERRESTRIALS፣ ሰውን ስለሚተኩ ሮቦቶች፣ ሰውና እንስሳ ስለሚመስሉ ፍጡሮችና እነዚያም ደግሞ ከኛ ከሰው ልጆች የተሻሉ መሆናቸውን  ነው። StarWars እና Independence Day የሚባሉት ፊልሞች ብቻ እንኳን ለዚህ በቂ ምሳሌዎች ናቸው።    በ2016 ብቻ የሚከተሉት 13 ፊልሞች የተሰሩትና የቀረቡት በዚህ ርዕስ ላይ ነው፤ Moonwalkers, The Fifth Wave, Lazer Team, The Last Man on the Moon, The Little Prince, Batman v Superman: Dawn of Justice, Independence Day: Resurgence, Star Trek Beyond, The Space Between Us, Rogue One, Passengers እነዚህና ከነሱም በፊት የወጡ ፊልሞች፣ የሚናፈሰው ዜናና ለልጆቻችንም በየትምህርት ቤቱ የሚሰጠው ቀልድ መሰል ትምህርት ዓላማቸው አንድ ነው። ይህም ዓላማ ጌታ አምላካቸውን በሚገባ የማያውቁ ክርስቲያኖችን ጨምሮ የዓለም ህዝብ ሃሰተኛውን ክርስቶስን እንዲቀበሉ ልባቸውን ለማዘጋጀት ነው። በሚቀጥሉት ትምህርቶች ይህንን በተመለከተ የበለጠ ዝርዝርና ክርስቲያኖች እንዴት ከዚህ ስህተት መጠበቅ እንደምንችል መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገረውን መሰረት አድርገን እንማራለን። እስከዚያ ግን መደንገጥ ወይም መታወክ የለብንም። እኛ ክርስቲያኖች ይህንን ሁሉ በቁጥጥሩ ስር ያደረገውን፣ ድል የነሳውን ኢየሱስ ክርስቶስን ስለተቀበልን በሚመጣው ነገር ሁሉ ድል አድራጊዎች ነን። የእግዚአብሔር ቃል የገለጸልንን እውነት ሁሉ ለማወቅ መትጋት ግን ያስፈልጋል። ጌታ ይባርካችሁ። አዘጋጅና አቅራቢ ዶ/ር በፈ ቃዱ ብርሃኑ አድማሱ

ዘጋጅታችሁ ኑሩ፣ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና፣ ማቴዎስ 24፤44 ትምሕርት ቁ 1 እና 2

ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፣ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና፣ ማቴዎስ 24፤44  ትምሕርት ቁ 1 እና 2
መጽሐፍ ቅዱስን በጥሞና የሚያነብና የሚያጠና እንዲሁም አምላኩንና ጌታውን የሚወድና ለመታዘዝ የሚተጋ ክርስቲያን ሁሉ ከምንም በላይ የሚናፍቀው ነገር ቢኖር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ሲመለስና ይህንን እየተተራመሰ ያለውን ፍጥረተ ዓለም ከጥፋት ታድጎ በጽድቅና በእውነት ሲነግስ ማየት ነው። የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ታላቁ ተስፋም ይኽው የጌታ ዳግም ምጽዓትና ለዘለዓለም መንገስ ነው። ታዲያ ክርስቲያን የሚናፍቀውን ይኼንን የጌታን ዳግም ምጽዓት እጅግ የሚፈሩትና እንዳይመጣም የሚሹና ቢቻላቸውም ሊያስቀሩት የሚጥሩም አሉ። አንዳንዶቹም እነሱ ራሳቸው ክርስቶስ ነን ይኸው መጣን በማለት ክርስቲያኖችን ለማሳሳት እንደሚሞክሩና ብዙዎችንም አሳስተው እንደሚወስዱ ጌታችን ራሱ በወንጌል አስተምሮአል። ታዲያ መቼ ነው ጌታ የሚመለሰው፣ ቀኑ መቃረቡንስ እንዴት ነው የምናውቀው የሚለው ጥያቄ የኛ ብቻ ሳይሆን ከጌታ ጋር በአካል በምድር ላይ አብረው የነበሩት የሐዋርያትም ያነሱት ነበር። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለዳግም ምጽዓቱ በወንጌል ውስጥ ካስተማረባቸው ብዙ ቦታዎች መካከል ትልልቆቹ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 24፣ የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 13 እና የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 21 ናቸው። በነዚህ ሶስት ዋና ዋና በሚባሉ የዳግም ምጽዓቱ ትምህርቶች ውስጥ ደቀ መዛሙርቱ በሚገባ እንዲያስተውሉ ጌታ ያስተማረው ትምህርት በሁለት አምድ በሚሆኑ መሰረታዊ ነገሮች ውስጥ ሚዛኑን የጠበቀ ነው ለማለት ይቻላል። የመጀመሪያው የእውነት አምድ ክርስቲያኖች ሁሉ “እኔ ክርስቶስ ነኝ” ዘመኑ ቀርቦአልና ይኽው መጥቻለሁ ከሚሉ ሃሰተኛ ክርስቶሶችና ሃሰተኛ ነቢያት እንዲጠበቁ ጌታ ማስጠንቀቁ ነው። ሁለተኛው አምድ ደግሞ ክርስቲያን ነኝ የሚል ሰው ሁሉ “ጌታ እስኪመጣ ይዘገያል” በሚል እንዝህላልነት፣ በዓለማዊነትና በስጋዊነት ኑሮ ተዘፍቆ የጌታ ቀን በድንገት እንዳይመጣበት ማስገንዘቡ ነው። ስለዚህ የጌታን ዳግም ምጽዓት በተመለከተ እያንዳንዱ ክርስቲያን በግሉም ሆነ የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን እንደ አንድ አካል በነዚህ በሁለቱ ሚዛን ጠባቂ የእውነት ዓምዶች መካከል በመቆም ታላቁን የወንጌል ተስፋ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ዳግም ምጽዓት ማወጅ፣ ማስተማርና ለመምጣቱም ተዘጋጅተው መኖር አለባቸው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ተነስቶ ካረገ ሁለት ሺህ ዓመት ሊሆን የቀረው ትንሽ ነው። የጌታ ሐዋርያት በምድር ላይ ከነበሩባቸው ከመጀመሪያው ምዕተ ዓመትና ዓመታትና ከዚያም በሚቀጥሉት ብዙ ምዕተ ዓመታት የነበሩት ክርስቲያኖች በነሱ ዘመን ጌታ ይመለሳል ብለው ተስፋ በማድረግ ይኖሩ ነበር። ይህንንም በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተጻፉት የሐዋርያት መልእክቶችና በቤተ ክርስቲያንም ረጅም ታሪክ ውስጥ ተጽፎ እናገኘዋለን። ታዲያ ለምንድር ነው በዚህ እኛ ባለንበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች ስለ ጌታ ዳግም ምጽዓት ብዙም የማንማረው፣ የማንሰብከው? ለዚህ ጥያቄ መልሱ በዚያው በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ አለ። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ሙሽራን በሚጠብቁ ሰዎች ምሳሌ በማድረግ በማቴዎስ ምዕራፍ 25 ከቁጥር 1 እስከ 13 ድረስ ባስተማረው ትምህርት ላይ ዘመኑ እየረዘመ ሲሄድ ብዙ ክርስቲያኖች ጌታ ከመምጣት የዘገየ መስሏቸው እንደሚዳከሙና፣ ሳያስቡት በድንገት ሲመጣም ብዙ ውካታ እንደሚሆን ገልጿል። በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 24 ላይ ደግሞ የሱ መምጣት በኖህ ዘመን የነበረውን ሁኔታ እንደሚመስል ጌታ በግልጽ አስተምሮአል። ስለዚህ የጌታ ዳግም ምጽዓት መድረሱን የምናውቅበት አንዱ መንገድ በኖህ ዘመን የነበረውን ሁኔታ በሚገባ ማስተዋል ነው ማለት ነው። በሚቀጥሉት መልዕክቶቼ ላይ ይህንን በተመለከተ አጠር አጠር ያሉ መረጃዎችን ከእግዚአብሔር ቃል፣ ከረጅሙ የቤተ ክርስቲያን ታሪክና እንዲሁም ደግሞ በትምህርቱና በምርምሩ ዓለም ካሉ ግኝቶችና ተጨባጭ ማስረጃዎች በማገናዘብ አቀርባለሁ። የበለጠ ዝርዝር ትምህርቶችን ለማድረግ የምትፈልጉ ደግሞ በየወሩ የሚወጣውን የመለከት ድምጽ መጽሔትን ተከታተሉ። በመጽሔቱ ላይም ለማቅረብ የሚረዝሙ ነገሮችን በተመለከተ ደግሞ ተጨማሪ ማስረጃ የሚሰጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችንና ሌሎች መጻህፍትን የሚያመላክት መረጃ በመጽሔቱ ላይ ይሰጣል። እስከዚያው ድረስ ግን በጸሎትና በጥሞና ከላይ የተጠቀሱትን ስለዳግም ምጽዓቱ ጌታ ያስተማረባቸውን ክፍሎች አንብቡ። የጌታ መምጣት እጅግ በተቃረበበት ዘመን ውስጥ ነው የምንኖረው። ቃሉ በእጃችን ሆኖ፣ የጌታ ቀን እንደ ሌባ ሊደርስብን አይገባም። ጌታ ራሱ እንዲህ ብሎናል፤
“ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ፣ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም። የኖኅ ዘመን እንደነበረ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና። በዚያች ወራት ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ፣ ሲያገቡና ሲጋቡም እንደነበሩ፣ የጥፋት ውኃም መጥቶ ሁሉን እስከወሰደ ድረስ እንዳላወቁ የሰው ልጅ መምጣት ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።” ማቴዎስ 24፤37
ከብዙ ሺህ ዓመታት በፊት ኖኅ የሚባለው ጻድቅ ሰው በምድር ላይ በሚኖርበት ዘመን፣ እግዚአብሔር አምላክ፤ ከሱና ከሰባት ቤተሰቡ፥ እንዲሁም ደግሞ ተመርጠው እሱ ወደ ሰራት መርከብ በመግባት ካመለጡት እንስሳት በስተቀር፤ የሰውን ዘርና እንስሳትን በሙሉ በውሃ እንዳጠፋ መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል።  የጥፋት ውኃ ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም ሃይማኖቶች፣ በአገሮችና ትውልዶች ታሪኮችም ውስጥ በስፋት የተዘገበና የሚነገር እውነታ ነው። የጥፋት ውኃ ምድርን ሁሉ አጥለቅልቆ ታላቅ ጥፋት መፍጠሩ ዛሬ በአርኪዎሎጂ እና በሌሎችም ሳይንሳዊ የምርምር መስኮችም ጭምር ተረጋግጧል። የጥፋትን ውኃ ታሪክ በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 6፣7፣ 8 እና 9 ላይ እናነባለን።
ለምንድ ነው እግዚአብሔር የምድርን ሕዝብና እንስሳት ሁሉ በውኃ ለመደምሰስ የወሰነው የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ በተለምዶ የሚነገረንና የተማርነው ነገር ቢኖርበዚያን ዘመን ኃጢዓት ስለበዛ ነው የሚል ብቻ ነው። እንደሌሎቹ ብዙዎች የብሉይ ኪዳን ክፍሎች ሁሉ ይህም ክፍል ጠለቅ ያለ መንፈሳዊ ትምህርት አይሰጥበትም። ከኖህ ዘመን በኋላና እስከ ዛሬም ድረስ በምድር ላይ ከምናየው ኃጢዓት የበለጠ ምን ዓይነት ኃጢዓት ቢሰራ ነው ጌታ ምድርን ፈጽሞ ለማጥፋት የሰወነው ብለን መጠየቅ ያሻል። መጽሐፍ ቅዱሳችንን ቀስ ብለን ካጠናንና በምድርም ሁሉ ላይ ያለውን መረጃና እውቀቶች ከመረመርን ለዚህ ከባድ ጥያቄ መልሱን ብዙም ሳንደክም እናገኛለን። በርግጥም በኖህ ዘመን እጅግ የከፉ ኃጢዓቶች ተሰርው ነበር። እነዚያ ኃጢዓቶች ግን እኛ በተለምዶ ኃጢዓት ብለን የምንላቸው ብቻ ሳይሆኑ መሰረታዊ የሆኑትን የጌታ አምላክን ሰማያዊና ምድራዊ የፍጥረት ሥርዓቶች ሁሉ የጣሱና ፍጥረትን ለማጥፋት የታቀዱ ነበሩ።
በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች ስለ ኃጢዓት ያለን መረዳት ጠባብና በአብዛኛውም በአሰርቱ በሙሴ በተሰጡት ትዕዛዛት ላይ ብቻ ያተኮረ ነው። ኃጢዓት ማለት በመሰረቱ ዐመጽ ነው፣ በጌታ አምላክና በስርዓቱ ላይ ማመጽ። ኃጢዓት ማለት ጌታ አምላክ ፍጥረቱ እንዲከተለው የዘረጋውን ሥርዓት መቃወምና ማፍረስ ነው። አሰርቱ የሙሴ ትዕዛዛት ኃጢዓትን በሙሉ አይገልጹም። የኃጢዓትን ምንነት ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስን በሙሉ በሚገባ መረዳት ያስፈልገናል። ለምሳሌ፣ የፍትህ መጓደልና ተገቢ ያልሆነ አድልዎ ጌታ አምላክን እጅግ የሚያስቆጣው በደል ነው። እንዲሁም ደግሞ ጌታ እግዚአብሔር ምድርንና ሰማይን፣ በተለይም ደግሞ እንስሳትንና ተክሎችን ሁሉ በፈጠረ ጊዜ ፍጥረታትን በጾታና በዘር በዘራቸው ከፋፍሎ ነው የፈጠራቸው። እያንዳንዱ እንስሳና ተክል የራሱን ፍሬ እንዲያፈራ በየዘሩ ወገን ውስጥ እንዲባዛ ጌታ አምላክ አዝዟል። በዘፍጥረት 1 ከቁጥር 11 እስከ 12 ድረስ ተክሎችን በየወገናቸው እንደ ፈጠረ እንማራለን። በዚሁ በዘፍጥረት 1 ከቁጥር 20 እስከ 22 ደግሞ የአየር፣ የምድርና የባህር እንስሳትን ፈጥሮ እያንዳንዳቸው በየወገናቸው እንዲበዙና እንዲባዙ ትዕዛዝን ሰጠ። ይህም ማለት እያንዳንዱ የተክልና የእስንሳ ዘር መባዛት ያለበት ጌታ በመደበለት በየወገኑ ውስጥ ብቻ ነው ማለት ነው።
በፍጥረት መጀመሪያ ላይ ጌታ አምላክ የነበረው አላማ ይህ መሆኑን ደግሞ ከጥፋት ውኃ በኋላ ብዙ ቆይቶ በሙሴ በኩል በሰጠው ህግ እንዲህ ሲል አረጋግጧል፤
“ሥርዓቴን ጠብቁ። እንስሳህ ከሌላ ዓይነት ጋር አይደባለቅ፥ በእርሻህም ሁለት ዓይነት ዘር አትዝራ፣ ከሁለት ዓይነት ነገር የተሰራ ልብስ አትልበስ።” ዘሌዋውያን 19:17 እና 18።
የሰው ልጆችም ደግሞ ለጾታቸውና ለሰብዓዊነታቸው ተገቢ በሆነ ባህርይ ብቻ እንዲገዙ አዝዟል። ፍትወተ ሥጋን በተመለከተ ለምሳሌ ጌታ አምላክ ወንድ ከወንድ ጋር፣ ወይም ሴት ከሴት ጋር ፍትወተ ሥጋን እንዳይፈጽሙ፣ እንዲሁም ደግሞ አንድ ወንድ ወይም ሴት ከእንስሳ ጋር ፍትወተ ሥጋ እንዳይፈጸሙ እንዲህ ሲል አዝዟል።
“ከሴትም ጋር እንደምትተኛ ከወንድ ጋር አትተኛ፣ ጸያፍ ነገር ነውና። እንዳትረክስባትም ከእንስሳ ጋር አትተኛ፣ ሴት ከእርሱ ጋር ትተኛ ዘንድ በእንስሳ ፊት አትቁም፥ የተጠላ ነገር ነውና።” ዘሌዋውያን 18፤22 እና 23።
ከእግዚአብሔር ሌላ አማልክት የሚባሉትን ማምለክና ለዚህም አምልኮ ህጻናትን መስዋእት ማቅረብ እጅግ የከፋ ኃጢዓት መሆኑን በዚሁ በዘሌዋውያን 18 ላይ በማስተማር ጌታ አምላክ የእስራኤል ልጆች ይህንን እና ከላይ የተጠቀሱትን ኃጢዓቶች ቢያደርጉ ምድሪቱ እንደምትተፋቸው እሱም እንደሚያጠፋቸው አስጠንቅቋቸዋል።
በኖኅ ዘመን ምድርን ፈጽሞ እስኪያጠፋ ድረስ ጌታ አምላክን ያስቆጣውን ዓመጽ የፈጸመው የሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን የሰማይ ልጆችም (በዘፍጥረት 6 ላይ የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉ ፍጥረታት)  ነበሩ።  ይህ ዓመጽ እጅግ የከፋና የፍጥረትን ምንነት በተለይም የሰውን ዘር ፈጽሞ ለማጥፋት የተቃረበ ዓመጽ ነበር። አስተውለን ካነበብነው መጽሐፍ ቅዱስ የሆነውን ነገር በግልጽ ያስረዳናል። ስለዚህም የሚመሰክሩ ሌሎች እጅግ ብዙ የታሪክ፣ የአርኪዎሎጂ፣ የህብረተሰብና የሌሎች ሃይማኖቶች መረጃዎችም አሉ። ለዚህ ለጥፋት ውኃ ፍርድ ዋነኛ መንስኤ ስለሆነው የዓመጽ ሁሉ ዓመጽና ከዚያም ስለተከተሉት ነገሮች በዘፍጥረት ምዕራፍ 3 እና ምእራፍ 6 ላይ የተጻፉትን በቅርብ ማጥናት ያሻል። ዘፍጥረት 6ን ከማጥናታችን በፊት ግን ከጥፋት ውኃ በፊት በምድር ሁሉ ተሰርተው የነበሩ እጅግ አስደናቂና አስገራሚ የሚባሉ፣ የሰው ልጅ ዛሬም እንኳን ባለው የእውቀት ደረጃና ቴክኖሎጂ ሊሰራቸው የማይችሉ ብዙ ህንጻዎች፣ ሃውልቶች፣ ማዕከሎችና በምድር ሁሉ ያሉ የጥንት ከተማዎችንና የኗሪዎቹን ቅሪቶች እንመለከታለን። ከነዚህም መካከል የግብጽ ፒራሚዶች፣ በሊባኖስ ባአልቢክ የሚገኘው የጁፒተር ቤተ መቅደስ ቅሪት፣ በካምቦዲያ የሚገኘው የአንግ ኮር ዋት ቤተ መቅደስ ቅሪት፣ በሜክሲኮ፣ በፔሩ እና በሌሎችም የደቡብ አሜሪካ አገሮች የሚገኙ እጅግ ብዙ ፒራሚዶች፣ ቤተ መቅደሶች፣ ታላላቅ የጥንት የአምልኮና የስፖርት ማእከሎች፣ ከተማን ከከተማ እና አገርን ከአገር የሚያገናኙ የመሬት ውስጥ ዋሻዎችና መንገዶች እንዲሁም ባህር የከደናቸው ከተሞችና ቅሪቶች ይገኙበታል። እንዲሁም ደግሞ ቁመታቸው ከ3 እስከ 6 ሜትርና ከዚያም በላይ የሆኑ ግዙፍ ሰዎችና ሰው መሰል ፍጥረቶች ዓጽሞችና ይጠቀሙባቸው የነበሩ ቁሶችና ቅሪቶች በዓለም ሁሉ መኖራቸው ተረጋግጧል። እነዚህ ሁሉ እርስ በርሳቸውም ሆነ በኖኀ ዘመን ከመጣው የጥፋት ውኃ ጋር፣ ከዚያም በበለጠ ደግሞ ከዚህ ከኛ ዘመንና ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽዓት ጋር ያላቸውን ግንኙነቶች በተመለከተ የሚቀጥሉ ትምህርቶችን ከፈል ከፈል አድርጌ አቀርባለሁ። እስከዚያ ድረስ ከላይ የተጠቀሱትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፣ በተለይም ደግሞ ዘፍጥረት ምእራፍ 1፣ ምእራፍ 6 እስከ 9፣ ዘሌዋውያን 18 እና 19ኝን አንብቡ። አዘጋጅና አቅራቢ፤ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ


ከሁሉም የላቀ የአዲስ ዓመት ውሳኔ ፥ የሕይወትን እንጀራ መብላት፣ የሕይወትን ውኃ መጠጣት

ከሁሉም የላቀ የአዲስ ዓመት ውሳኔ ፥ የሕይወትን እንጀራ መብላት፣ የሕይወትን ውኃ መጠጣት

ከምዕራቡ ዓለም የአዲስ ዓመት አከባበር ወጎችና ልማዶች አንዱ እያንዳንዱ ሰው በአዲሱ ዓመት ይህን ወይም ያንን ማድረግ አለብኝ ወይም ማድረግ እፈልጋለሁ ማለትና ጥቂት ነገሮች በመምረጥ ከራሱ ጋር ቃል መግባት ነው። አንዳንዱ ሰው ጤናውን ለማሻሻል የአካል እንቅስቃሴን መጀመር ሲሻ፣ ሌላው ኑሮውን ለማሸነፍ የተሻለ ሥራን ለመያዝ ያቅዳል፣ አንዱ የተሻለ ትምህርትን ለመጀመር ሲያስብ፣ ሌላው ደግሞ  ትዳር ለመመስረት ይነሳል። ልጅ የሌላቸው ልጅ ለመውለድ ሲዘጋጁ፣ ልጆች ያሏቸው  ደግሞ ልጆቻቸውን በተሻለ መንገድ ለማሳደግ ቃል ይገባሉ። ሌሎች ደግሞ ሌሎች እቅዶችን ያቅዳሉ፣ ይፈልጋሉ ውሳኔንም ያደርጋሉ።
እቅድ መልካም፣ ውሳኔም ጥሩ ነው። ታዲያ የሚፈልጉትን ሁሉ ማድረግ አስቸጋሪ ወይም ከባድ ነውና፣ ውሳኔዎችን ቅደም ተከተል በማስያዝ አንዱ ወይም ሁለቱ ላይ ማተኮር እጅግ ይጠቅማል። ከውሳኔዎች ሁሉ በላይ የሚበልጥ ውሳኔ፣ ከምርጫዎችም በላይ የሚበልጥ ምርጫ ደግሞ አለ። መጀመሪያ እረኛ የነበረና የወንድሞቹ ሁሉ ታናሽ ወንድም ቢሆንም የኋላ ኋላ የእስራኤል ንጉስና የእግዚአብሔር የልብ ሰው የተባለለት ዳዊት ገና በልጅነቱ ነበር ከምርጫዎች ሁሉ በላይ የሆነውን ምርጫ የመረጠው። ሌሎች ፍላጎቶቹንም ለዚህ ለዋነኛው ምርጫው የበታች አድርጎ አስቀመጣቸው። ያንን ታላቁን ምርጫውን እንዲህ ሲል ነው ዳዊት የገለጠው፤
“እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በህይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፣ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።” መዝሙር 27፥4 
ዳዊት አምላኩን ለማወቅ፥ ወደሱም ተጠግቶና እሱን ደስ እያሰኘ ለመኖር የነበረው መሻትና ውሳኔ እጅግ ጠንካራ ስለነበር ይህ ፍላጎቱን በረሃብና በጥማት መልክ ይገልጠው ነበር። በመዝሙር ምዕራፍ 42 ላይ ለምሳሌ እንዲህ ይላል፤
“ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ አቤቱ  እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች፣ መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ?” መዝሙር 42፤1ና2
በዚህም ሕይወት ሆነ በሚመጣው ዓለም እግዚአብሔርን እንደማወቅና ወደርሱም ተጠግቶ በፍቅሩ ሥር እንደመኖር አስደናቂ፣ አስደሳች፣ አርኪና፣ ዘላቂ ነገር የለም። በአዲሱ ዓመት ካወጣናቸው እቅዶችና ውሳኔዎች ሁሉ ዋነኛው እግዚአብሔርን ማወቅ፣ በበለጠ ወደርሱ መጠጋት እና እግዚአብሔርም በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለኛ የገለጠውን ፍቅር መለማመድ፣ እሱን መታዘዝና በረከቱንም ለመቀበል መዘጋጀት ዋነኛዎቹ ካልሆኑ ሌሎቹ ምርጫዎቻችን ትክክለኛውን ቅደም ተከተል አልያዙም። የምናገኘውን ነገር ሁሉ አንድ ቀን ጥለነው እንሄዳለን። እግዚአብሔርን ችላ ብለን የምንሰበስበው ሁሉ የግድ አንድ ቀን ይበተናል። የምርጫችን ሁሉ ቁንጮ፣ የጥማታችንና የመሻታችን ሁሉ ዋነኛው ትኩረት ጌታ እግዚአብሔር ከሆነ ግን በዚህች አጭር ሕይወትም ሆነ በሚመጣው ዘለዓለም እጅግ የተደሰትን፣ ሙሉ ሰላም ያለንና የተባረክን ሰዎች እንሆናለን።
እውነተኛው የሕይወት እንጀራ፣ የሚያረካው የሕይወት ውኃ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህንን እንጀራ መብላትና፣ ከዚህም ውኃ መጠጣት ከአዲሱ ዓመት ውሳኔዎቻችን ሁሉ ዋነኛው ቢሆን ለዘላለም አትራፊ እንጂ የከሰርን አንሆንም። ይህ ጌታ ደግሞ እኛ ከምንፈልገው ይልቅ ፈልጎን እኛ አለንበት ድረስ መጥቷል ዛሬም ይመጣል። ባለንበት የእድሜ፣ የእውቀት፣ የኢኮኖሚ፣ የጉልበት፣ የጤና ሁኔታና ደረጃ ሊያገኘን ይናፍቃል። ይህች ቀን በምድር ላይ የቀረን እድሜአችን የመጀመሪያይቱ ቀን ናት። ታዲያ በዚህች ቀን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በነቢዩ በኢሳይያስ ቃል እንዲህ ሲል ይጠራናል፤
“እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁ ኑና ግዙ፣ ብሉም፥ ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት ግዙ። ገንዘብን እንጀራ ላይደለ፣ የድካማችሁንም ዋጋ ለማያጠግብ ነገር ለምን ትመዝናላችሁ? አድምጡኝ፣ በረከትንም ብሉ ሰውነታችሁ በጮማ ደስ ይበለው። ጆሮአችሁን አዘንብሉ ወደ እኔም ቅረቡ፣ ስሙ ሰውነታችሁም በሕይወት ትኖራለች፣ የታመነችውንም የዳዊትን ምሕረት፥ የዘላለምን ቃል ኪዳን ከእናንተ ጋር አደርጋለሁ። ” ኢሳይያስ 54፤1፥3
ክርስቲያንም ብንሆን ገና ያላመንንን ሰዎች ጌታ እግዚአብሔር በሱ በኩል ሊደረግ የሚገባውን ነገር ሁሉ ፈጽሞ ወዳዘጋጀው የዘላለም ሕይወት ድግስ በክርስቶስ ይጠራናል። በዛሬይቷም ቀን ሆነ በነዚህ በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያው ቀናት ምርጫችን ወደሱ መቅረብ ከሆነ ሌላው ነገር ሁሉ ሳይወድ በግድ ቦታውን ይይዛል። የያዘ ባይመስለንም ደግሞ በክርስቶስ ሆነን የዘላለሙን ሕይወታችንን ከያዝን ሌላውን ነገር ሁሉ በላቀና በከበረ መንገድ ሳንፍጨረጨር ለዘለዓለም እናገኘዋለን።
ስለዚህ የዚህ የአዲሱ ዓመት ዋነኛው ውሳኔያችን በልተነው እንደገና የማንራበውን የሕይወትን እንጀራ ለመብላት እና ጠጥተነው እንደገና የማንጠማውን የሕይወትን ውኃ ለመጠጣት ይሁን። ይህ የሕይወት እንጀራና የሕይወት ውኃ ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤
“ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፥ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም፥ በእኔ የሚያምንም ሁል ጊዜ ከቶ አይጠማም።” የዮሐንስ ወንጌል 6፥35
“መንፈሱና ሙሽራይቱም፤ ና ይላሉ። የሚሰማም፤ ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፣ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው (በነጻ፣ በጸጋ) ይውሰድ።” የዮሐንስ ራዕይ ምዕ 22 ቁ 17

አዘጋጅና አቅራቢ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ

ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬ በበረት ውስጥ የተኛ ህጻን አይደለም

ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬ በበረት ውስጥ የተኛ ህጻን አይደለም፣ ነፍሳችንን ለዘላለም ለማዳን የሚጠራን የፍቅር ንጉስ እንጂ
በዚህ ምድር ከምንለማመዳቸው ዘላቂ ደስታዎች ሁሉ ልዩ የሆነው የአዲስ ልጅ መወለድ ነው የሚለውን አባባል ብዙ ሰው ይስማማበታል። ደስታዎች ብለን የምንጠራቸው ሌሎች ነገሮች ሁሉ ከዚህ ዋነኛ ደስታ የሚመነጩ ናቸው ብንልም፣ ሃሳቡ የፍልስፍና ይምሰል እንጂ እውነት መሆኑ የግድ ነው። ምክንያቱም እኛ ሁላችንም ደስታን የምንለማመደው በመጀመሪያ ወደዚህ ደስታውን ወደምንለማመድበት ዓለም የመጣነው በልደት ስለሆነ ነው። ወቅቱ ስለሆነ እያከበርነው ያለነውን የጌታን ልደትም (CHRISTMAS) ከዚሁ የአዲስ ሰው ወደዚህ ዓለም መምጣት ጋር እጅግ የተቀራረበ አድርገን እንድንገምት ያደርገናል። በርግጥም የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ለሰው ልጆች ሁሉ ታላቅ ወንድም፣ አዳኝና ጌታ የሆነው ፍጹም ሰውና ፍጹም አምላክ መምጣት ነውና ታላቅ ደስታ ልንደሰት ይገባል። በክርስቶስ ልደት  ምክንያት ያገኘነው ደስታ ደግሞ ከሰባ፣ ከሰማንያ ወይም ከዘጠና ዓመት በኋላ በሃዘንና በእንባ ወደመቃብር በምንሸኘው በኛ በሟች የሰው ልጆች መወለድ ከምናገኘው ደስታ እጅግ የላቀና ዘላለማዊ ነው። ይህን እውነት ከተገነዘብን ታዲያ ደስታችንም እንዲሁ ዘላለማዊ ነው ማለት ነው።
ይህንን የገናን እና የፈረንጆቹን አዲስ አመት ፌሽታ ረስተን ወደተለመደውና ወደ ግራና ወደ ቀኝ እንደሸማኔ መወርወሪያ ወደሚወዘውዘን ኑሮአችን ከመመለሳችን በፊት ልንገነዘብ የሚገቡን ትልልቅና ዘላለማዊ ቁም ነገሮች አሉ። ከነዚህም አንዱና ዋነኛው ይህ ልደቱን ያሰብነውና ያከበርነው ልዩ ሰውና የእግዚአብሔር ልጅ ወልድ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ በዚህ ሰሞን እንደምናስበው አሁንም በቤተልሔም በረት ውስጥ በጨርቅ ተጠቅልሎ እረኞች ሊያዩት የሜመጡ ህጻን አይደለም። የዚህን የመሲሁን መምጣት በተመለከተ ትንቢትን ከተናገሩት ነቢያት አንዱ ነቢዩ ኢሳይያስ የዚያን፣ የዛሬ 2016 ዓመት ገደማ እንዲህ ብሏል፤
“ሕጻን ተወልዶልናል፣ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፣ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያጸናውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍጻሜ የለውም።” ኢሳይያስ 9፤6፥7
የመወለዱን የምስራች ካበሰረ በኋላ፣ ነቢዩ ወዲያውኑ ስለዚህ ህጻን የገለጸው አንዱ ቁም ነገር “አለቅነት” ሁሉ ወይም በዛሬው ዘመናዊ አማርኛ “የመንግስት የበላይ ገዢነት” ሥልጣን በሱ ትከሻ ላይ እንደሆነ ነው። መሲሁን ይጠብቁ የነበሩ ብዙዎቹ የእስራኤል ሕዝብ ይህንን “ገዢነት” ወይም “አለቅነት” የተረዱት በመካከለኛው ምስራቅ በምትገኘው አገራቸው ታሪክና ከነበሩበት የፖለቲካ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ ብቻ ነበር። የተወለደው ኢየሱስ ክርስቶስ በርግጥም በዳዊት ዙፋን ላይ ሆኖ በቃል ኪዳን የእግዚአብሔር ህዝብ በሆነው በእስራኤል ላይ የሚገዛ ቢሆንም፣ የመንግሥቱ ሥልጣን ግን በአንዲት አገር፣ አህጉር ወይም በምድርም ብቻ የተወሰነ አይደለም። መንግስቱ በዚህች በኛ ምድርና በላይዋ ባሉት አገሮችና፣ ድርጅቶች ሁሉ ላይ፣ ከዚያም አልፎ በሰማይና እኛ ሰብዓዊ ፍጡሮች በውስን ችሎታችን ልናውቃቸውና ልንደርስባቸው በማንችለው በቁሳዊና መንፈሳዊ ዓለማት ባሉ ፍጥረታትም ሁሉ ላይ ትገዛለች። በዚህ በምድራችን ላይ ለዘላለም ሊገዛ ያለው የክርስቶስ መንግስት ደግሞ እኛ የሰው ልጆች እንደምንመሰርታቸው በታሪክ እንዳለፉት፣ ዛሬ እንዳሉት ወይም ነገ ሊኖሩ እንደሚችሉት በፖለቲካ ሽኩቻ፣ በጦርነትና በተንኮል፣ በገንዘብ ብርታትና በማህበረሰባዊ ግፊት የሚመሰረት ወይም የሚጸና  አይደለም።
የክርስቶስ መንግስት ፍጹም ፍትህ፣ ጽድቅ፣ ሰላምና ፍቅር የሰፈነበት፣ ለስልጣንና ንብረት ክፍፍል ድርድር የማያስፈልግበት፣ ፍርድ ቤት፣ ፖሊስና ወህኒ የማያሻው፣ የአማካሪዎች ጉባኤና ምርጫ፣ ሰይፍና ጦር የሚረሱበት፣ በዘመንና በቦታ የማይወሰን ዘላለማዊ መንግሥት ነው። ይህን መንግሥት እውን ለማድረግ ደግሞ የዚህ መንግሥት ራስና ቁንጮ የሆነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እያንዳንዱን የመንግስቱን ዜጋ የሚመርጠው ኑ ገንዘብ አዋጡልኝ፣ ደግፉኝ በማለት ሳይሆን የኃጢዓታቸንን እዳ ራሱ በመስቀል ላይ ሞቶ ከከፈለና የምንወርሰውንም ግሩም ድንቅ ዓለም ራሱ ካዘጋጀ በኋላ ነው። ይህንን ጌታና አምላክ በቀጥታ ለማወቅ፣ ለማመንና ለመቀበል እድል የማይሰጠው የሰው ልጅ የለም። የመንግስቱ ዜግነትም የሚሰጠው ከነገድ፣ ከወገን፣ ከቋንቋና ከብሔሮችም ሁሉ ለመጡ ለትልልቆችና ትንንሾች፣ ባለጸጋዎችና ድሆች፣ ለመኳንንትና ተራ ሰዎች፣ ለተማሩና ላልተማሩም፣ ለወንዶችና ሴቶችም ሁሉ ነው። በክርስቶስ የማመንና የዘላለማዊው መንግሥት ዜግነት እድል የሚገኘው ደግሞ ሞኝነት በሚመስለው በኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መሰበክ የሚተላለፈውን የእግዚአብሔርን ቃል በማመን ነው።
የኢየሱስ ክርስቶስ የወንጌል መልእክት ሰማያዊና ዘላለማዊ ስለሆነ፣ እኛ ምድራውያን የሆንን ሰዎች ባሉን አምስት የስሜት ህዋሳት፣ በአእምሮ ችሎታችን፣ በእውቀታችን፣ በልምዳችንና ነገሮችን በማገናዘቢያ ተሰጥዎዎቻችን ብቻ ልረዳው አንችልም። የወንጌልን ሰማያዊ መልዕክት ሊሰማና ሊረዳ የሚችለው መንፈሳዊ ማንነታችን በኃጢዓት ምክንያት ሞቷልና። ውስጣዊው ማንነታችን (ነፍሳችን፣ ህሊናችን) ግን በጥልቅ ሊረካ በማይችል ጥማት ይሰቃያል። ብዙዎቻችን ታዲያ የነፍሳችንን ጥያቄና ጥማት አፍነን የራሳችንን ክብርና የሰውን ምስጋና ከመፈለግ የተነሳ የሰው ወግ የሰጠንን የከንቱ ውዳሴ ካባ ለብሰን ደስተኞች መስለን እንኖራለን። በዚያ በሚሞቀው ካባችን ውስጥ ሆነንም ታዲያ ነፍሳችን ወደፈጣሪዋ መጮኋን አታቋርጥም። ይኼ የገናው ህጻን ኢየሱስ ክርስቶስም ያንን የነፍሳችንን ጩኸት ይሰማል። ለያንዳንዳችን በግላችን፣ ለሰው ልጆች ሁሉም በጋራ የዛሬም ሆነ የነገ መልስ አልባ ጥያቄዎቻችን መልስ ያለው በዚህ አስደናቂ ሰውና አምላክ በኢየስስ ክርስቶስ እጅ ነው።

ክርስቶስ ዛሬ የሚጠራን ቤተልሔም ከተማ ባለች አንዲት የማረፊያ ሆቴል በከብቶች በረት ውስጥ ህጻን ሆኖ ተኝቶ ስጦታዎችን እንድናመጣለት ሳይሆን፣ በቀራንዮ መስቀል ላይ ስለኛ ሞቶ፣ የሞትን ኃይል ድል አድርጎ፣ በክብር እስኪመለስና ዘላለማዊ መንግስቱን እስኪመሰርት እንዲሁም እኛ ሁላችንም ንስሐ እስክንገባ ድረስ በትዕግስት ከሚጠብቅበት ከእግዚአብሔር አብ ዙፋን ቀኝ ሆኖ እንድናምነውና ከዘላለም ሞት እንድናመልጥ ነው። ለመንግሥቱ መገለጥም ቀንን ቀጥሮአል፣ እኛ መቼ መሆኑን አንወቅ እንጂ። ስለዚህ የገና ደስታችንን ድምቀቱ በቀኖች ማለፍና በኑሮ ውጣ ውረድ እየፈዘዘ ከመሄዱ በፊት የዚህን የገናውን ጌታ ጥሪ እንስማ። ክርስቶስን ያላወቅነው ሁሉ ንስሃ ገብተን ዛሬ እንቀበለው። የምናምነውና ነፍሳችንን አደራ የሰጠነው አማኞች ደግሞ በተሰጠን የዘላለማዊ ሰላም፣ የደስታና የተስፋ ኃይል በመበርታት የወንጌሉን የምስራች ላልሰሙ ሁሉ እንንገር። ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬ በበረት ውስጥ የተኛ ህጻን ሳይሆን፣ በክብር ተገልጦ የዘለዓለም መንግስቱን በፍጥረት ሁሉ ላይ ለመመስረት የሚጠብቅ የምድር ገዢዎች ሁሉ የበላይ ጌታ፣የመንፈሳዊውና የቁስ አካላዊውም ዓለም ሁሉ መስራችና ዘላለማዊ ባለቤት ነው። አዘጋጅና አቅራቢ ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ 

ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን

ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፣ እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ። ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብጹዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል፥ ቀርቦም ያገለግላቸዋል። ….. እናንተም ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፣ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና። ሉቃስ 12:35-40
ሁሉን ነገር ዛሬውኑ ልያዘው፣ ልጨብጠው በሚባልበት በዚህ ዘመን እንደ መጠበቅ ከባድ ነገር የለም። በተለይም ደግሞ በከፍተኛ የኢኮኖሚ ብልጽግናና የቴክኖሎጂ እድገት ላይ በሚገኙት አገሮች ውስጥ ዛሬ መጠበቅ እንደ ትልቅ መከራ ይቆጠራል። ኑሮ ከድመት ወይም ከሌሎች አደጋዎች ለማምለጥ የሚራወጡትን የአይጦች ውድድር ይመስላል። በርግጥም ደግሞ ይህንን ገደብ የለሽ ሩጫ ፈረንጆቹ የአይጥ ውድድር ወይም RAT RACE ይሉታል። ያላገኘ ለማግኘት፣ ያገኘ ደግሞ ባለው ላይ ለመጨመርና ያለውንም እንዳያጣ ለመጠበቅ ይዋከባል። እስቲ የመገናኛ እና የመረጃ መለዋወጫ መሳሪያዎችንና መረቦችን እንደ ምሳሌ እንውሰድ። የዛሬ አርባ አመት ገደማ በሰዎችም ሆነ በድርጅቶች መካከል ዋነኛው የመረጃ መለዋወጫ መንገድ ደብዳቤ መጻጻፍ ነበር። በአገራችን በኢትዮጵያ 15 ሳንቲም ከፍለን ደብዳቤ ጽፈን የምንልክባት እንደ ፖስታም፣ እንደወረቀትም እንደ ቴምብርም የምታገለግል ኤሮግራም የምትባል አንድ ፖስታ ቤት የሚሸጣት ወረቀት ነበረች። ድሃውም ሃብታሙም ከዘመድ አዝማድ ጋር በዚያች ትንሽ ወረቀት ይገናኝ ነበር። ታዲያ ተጽፋ ወደተፈለገችበት እስክትደርስ ድረስ አንዳንድ ጊዜ እስከ አንድ ወርም ትወስድ ነበር። በአብዛኛው የኢትዮጵያ ከተሞችና መንደሮች ስልክ ስላልነበር፣ አቅሙ ያለው ሰው እሷን ሊቀድማት የሚችለው ገንዘብ ከፍሎ በአውቶቡስ ተሳፍሮ በመሄድ ብቻ ነበር። እነ ቴሌክስና ቴሌግራም የሚባሉት ቴክኖሎጂዎች ዋጋቸው ውድ ስለነበር ስራ ላይ የሚውሉት ብዙ ገንዘብ ባላቸው ድርጅቶችና መንግስታት ለዚያውም አስቸኳይና አጭር የሆኑ መረጃዎችን ለመለዋወጥ ብቻ ነበር።
የዛሬ ሃያ አምስት ዓመት ገደማ ደግሞ ቴለክስና ቴሌግራም ኋላ ቀር ሆኑና ዘመናዊውና ፈጣኑ መሳሪያ ፋክስ (FAX) የሚባለው ሆነ። በፈረንጆቹ አቆጣጠር ከ1990ዎቹ አጋማሽ ላይ ጀምሮ እንደ ሰደድ እሳት በምድር ሁሉ መያያዝ የጀመረው የዓለም አቀፉ የግንኙነት መረብ (ኢንተርኔት) ሲመጣ ደግሞ እነ ቴሌክስ፣ ቴሌግራም፣ ፋክስና የቤት ስልክ ሳይወዱ በግድ መንገዳቸውን ወደ ሙዚየም ማቅናት ጀመሩ። ዘመናዊዎቹ ኢሜይልና ተንቀሳቃሽ ስልኮች,በመገናኛ አደባባይ ላይ ባለዘመኖች መሆን ጀመሩ። ባለፉት አስር በማይሞሉ ዓመታት ደግሞ እነ ኢሜይልም ከሳሎን ቤት ወደ ጓዳ ተገፉና፣ “መልእክት አሁኑኑ”  (INSTANT MESSAGING) የሚባለው የመገናኛ ዘዴ በተለይም ደግሞ በቀላሉ በኪስ በሚገቡ በብልጦቹ ስልኮች (SMART PHONES) አማካይነት ሩጫውን ያሸነፈ ይመስላል። ይህም አልበቃ ስላለ ታዲያ እንደነ GOOGLE፣ MICROSOFT እና APPLE የመሳሰሉ ድርጅቶች ችግሩ የሰው ልጅ ራሱ ቀርፋፋ ስለሆነ ነውና የሰውን ጭንቅላት ራሱን ከኮምፒውተር ጋር በማገናኘት የተሻሻለ ፍጥረት መስራት አለብን  ብለው በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብን በማፍሰስ የሰውን ልጅ ራሱን ኋላ ቀር የሚያደርግ የሰውና የኮምፒውተር ዲቃላ ለመፍጠር ሌሊትና ቀን እየሰሩ ነው፤ ብዙ ርምጃዎችንም አድርገዋል። ይህ ጥረታቸውም በመንግስታት በጀትም ሳይቀር ይደገፋል። ታዲያ ይኼ የሚያመራው ወዴት ይሆን? መጽሐፍ ቅዱስስ ስለዚህ ምን ይላል? ጌታ እግዚአብሔር ሳያውቀው የሚሆን አንድም ነገር የለምና በርግጥም መጽሐፍ ቅዱስ በመጨረሻው ዘመን እውቀት እጅግ እንደሚበዛና ሰዎችም ከስፍራ ወደ ስፍራ እንደሚራወጡ ይናገራል። ለምሳሌ ዳንኤል 12 ቁጥር 4ን ተመልከቱ። ጌታ ቢፈቅድ የዚህን ነገር የወደፊት አቅጣጫና የመጨረሻ ውጤት ወደፊት በሚወጡ አጫጭር መልእክቶችና በመለከት ድምጽ መጽሔትም ላይ እንነጋገርባቸዋለን።
ከላይ እንደተመለከትነው ዛሬ በሰው ዘር ታሪክ ያልነበሩ እጅግ ፈጣንና ለመጠቀም ብዙም የማያስቸግሩ የመነጋገሪያና የመረጃ መለዋወጫ ዘዴዎች አሉን። እነዚህ ሁሉ ግን በሰው ልጆች መካከል ያለውን የልብና ያለመግባባት ችግር ሊፈቱ አልቻሉም። መነጋገሪያው ፈጣን መሆኑ ክፋት ባይኖረውም፤ ችግሩ ያለው አሁንም የሰው ልብ ጋ ስለሆነ ቴክኖሎጂ እንደ ድምጽ ማጉሊያ የሰውን ልብ ጫጫታ በፍጥነትና በቀነሰ ዋጋ ያጓጉዘዋል እንጂ ጫጫታውን መልክ ወዳለው ንግግር አይለውጠውም ወይም ለያንዳንዱ የሰው ልብ ጩኸት መልስ ሊሆን አልቻለም፣ አይችልምም። ይህን ያልተረዳ የሰው ልጅ ግን ዛሬም ቢሆን  ችግሩ የስልኩ፣ የኢንተርኔቱና የቴክስቱ መንቀርፈፍ ነው ብሎ ያጉረመርማል።

ታዲያ በክርስቶስ ዳግመኛ የተወለድን ክርስቲያኖችስ ዛሬ የምናሳድደው ምን ይሆን። አዳኛችንና ጌታችን የሰጠንን ወንጌልን ለሌሎች የማድረስ አደራና ትዕዛዝ ለመወጣት ምን ያህል እንቸኩላለን፣ እንተጋለን? በደሙ ኃጢዓታችንን ካነጻ በኋላ ወደ ሰማይ የሄደውንና ተመልሼ እመጣለሁ ያለንን ጌታ መጠበቁንስ ምን አድርገነው ይሆን? ጌታ ራሱ፣ ነቢያትና ሃዋርያትም እንዳስተማሩት ይህ ጌታ ባላሰብነው ሰዓትና ጊዜ ተመልሶ ይመጣል። በሰማይ ደመና፣ በመላእክትና በቅዱሳን ታጅቦ በክብር ይገለጣል። ሊሞላ የማይችለውን ስጋዊና ምድራዊ ነገር ብቻ ወደው ጌታን የገፉትና እምቢ ያሉት የምድር ወገኖች ሁሉ ጌታ በድንገት ሲገለጥ ዋይ ዋይ ይላሉ። (ራዕይ 1:6) ወንጌልን ያመንን እኛ ግን የጌታ ቀን እንደ ሌባ ይደርስብን ዘንድ በጨለማ አይደለንም።(1ኛ ተሰሎንቄ 5:4) የእግዚአብሔርን ቃል በልባችን እየሞላን፣ ለመንፈስ ቅዱስ ድምጽም ደግሞ ልባችንን ሳናደነድን በጌታ ያገኘነውን የህይወት ብርሃን እያበራን፣ በዚህ አለም ኮተታ ኮተት ልባችን ሳይያዝብን ተግተን ሙሽራውን ኢየሱስን ልንጠብቀው ይገባል። እሱ ለሙሽራይቱ ቤተ ክርስቲያን ስፍራን ሊያዘጋጅ ሄዷል። እኛ የሙሽራይቱ አካላት የሆንን ደግሞ የግል ህይወታችንም ሆነ ቤተ ክርስቲያን ሙሽራው በሚገለጥበት ጊዜ ያለውርና ያለነቀፋ ሆነው እንዲገኙ ተዘጋጅተን እንድንጠብቀው ታዘናል። ስለዚህ ጌታችን በመጣ ጊዜ መብራታችን እንደበራና ወገባችንም እንደታጠቀ ሆነን በሩን ሲያንኳኳ ልንከፍትለት እንዘጋጅ። “ይህን የሚመሰክር አዎን በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ቶሎ ና።” ራዕይ 22:20  አዘጋጅና አቅራቢ: ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ

ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ ወደ ጦርነት መውጣት

ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ ወደ ጦርነት መውጣት
በሚገፋችሁ ጠላት ላይ በምድራችሁ ወደ ሰልፍ (ጦርነት) ስትወጡ ከፍ ባለ ድምጽ መለከቶቹን ንፉ፣ በእግዚአብሔርም በአምላካችሁ ዘንድ ትታሰባላችሁ፣ ከጠላቶቻችሁም ትድናላችሁ። (ዘሆልቁ 10፤9)
የእግዚአብሔር ህዝብ እስራኤል ወደ ጦርነት እንዲወጡ ጌታ ይፈቅድላቸው ወይም ያዝዛቸው የነበረው በሁለት ምክንያቶች ብቻ ነበር። የመጀመሪያው ምክንያት እርሱ እንዲወርሱት የሰጣቸውን ምድር ለመውረስ ወደ ከነዓን ምድር በሚገቡበት ጊዜ የግድ በዚያ የነበሩትን ዓመጸኛ እና በአጋንንታዊ ሥርዓት ስር ይኖሩና የሰይጣን ተባባሪ የሆኑትን ህዝቦች ለማጥፋት ነበር። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ እስራኤል ወደ ተስፋው ምድር ሲሄዱ በመንገድ ላይ ሊያጠቋቸው ከተነሱ እንደ አማሌቃውያን ካሉ ህዝቦች ወይም ደግሞ የተስፋውን ምድር ከወረሱ በኋላ ሊያጠፉአቸው ወይም ሊዘርፏቸውና ባሪያ ሊያደርጓቸው ከሚመጡ እንደ ፍልስጥኤማውያን፣ ሶርያውያንና ምድያማውያን ካሉ ጠላቶቻቸው ራሳቸውን ለመከላከል ነበር። አንዳንድ ጊዜ ግን የተለያዩ የእስራኤል መሪዎች ትክክል ያልሆኑ ጦርነቶች በራሳቸው ፈቃድ እያስነሱ ይዋጉ ነበር። ብዙውን ጊዜም እነዚህ ጦርነቶች የሚያመጡት ውጤት እልቂትና ጥፋት እንዲሁም ሽንፈት ነበር። በአዲስ ኪዳን ዘመን (በዚህ በኛ ዘመን) የእግዚአብሔር ህዝብ ደግሞ ክርስቲያኖችና ናቸው። የክርስቲያን ጦርነት ደግሞ መንፈሳዊ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል። በምድር ላይ የምናያቸውው በአገሮች፣ በህዝቦችና በግለሰቦችም መካከል የሚፈጠሩ ግጭቶችና ጦርነቶች ሁሉ ዋነኛው መንስኤዎቻቸው የሰው ልጅ ኃጢዓትና አለመታዘዝ እንዲሁም ደግሞ የሰውን ዘር ለማጥፋትና ለማመሰቃቀል ሌትና ቀን ተግተው የሚሰሩ የዚህ የጨለማው ዓለም መንፈሳዊ ገዢዎች የሚያደርጉት ትግል ነው።
በብሉይ ኪዳን በእስራኤልና በእስራኤል ጠላቶች መካከል የተካሄዱት ጦርነቶች በአዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች ከጨለማው መንፈሳዊ ዓለም ኃይላት ጋር ለሚያካሂዱት ጦርነት እንደ ጥላና ምሳሌ ናቸው። እግዚአብሔር አምላክ ህዝቡን ወደ ጦርነት ውጡ ብሎ በሙሴ፣ በኢያሱ፣ በዳዊት፣ በጌዴዎን ወይም በሌሎች መሪዎች በኩል ትዕዛዝና መመሪያ በሰጠበት ጊዜ፣ ህዝቡና መሪዎቹ ደግሞ የጌታን ትእዛዝ በትክክል ከተከተሉ ጦርነቱ ሁል ጊዜ የሚደመደመው በድል ነበር። ጌታ እግዚአብሔር ራሱ ሰላምና የሰላምም አምላክ ነው። ሞትን፣ ጦርነትንን እልቁትን ወደዚህ ዓለም ያስገባው ግን በትዕቢት ተነፍቶ ጌታ አምላክን እተካለሁ ብሎ ተነስቶ የነበረው ዲያብሎስ፣ ሰይጣን፣ ዘንዶና የቀደመው እባብ ተብሎ በተላያዩ ስሞች በመጽሐፍ ቅዱስ የሚጠራው ሉሲፈር የሚባለውና ከክብሩ የተጣለው ኪሩብ ነው። በዚሁ በሰይጣን ተታልሎ ክብሩንና ህይወቱን በውሸት የለወጠው የሰው ልጅም በዚህ የእልቂት አገንዳ ውስጥ ተባባሪ ሆኖ ይሰራል። የእውነተኛ ክርስቲያን ጦርነት ግን ይህንን ሰይጣን የሚያካሂደውን የፍጅትና የእልቂት አጀንዳ ለመመከትና ሰዎች ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን ከዘላለማዊ ሞት እንዲያመልጡ ነው። ይህ ሊሆን የሚችለው ደግሞ ህዝቦች በሰላም መኖር ሲችሉና የክርስቶስ ወንጌልም የሚሰበክበት ሁኔታ ሲፈጠር ነው። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ደዘመዛሙርቱን ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፣ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ ብሎ ሲልካቸው፣ እርሱ ራሱም ደግሞ ከነሱጋር ሁልጊዜ እንደሚሆን ቃል ገብቶአል።

ስለዚህ በዚህ ዘመን የንጉስ ካህናት፣ ቅዱስ ህዝብና ለርስቱ የተለየ ወገን አድርጎ እግዚአብሔር የጠራን ክርስቲያኖች ሁሉ አምላካችን ላሰለፈን መንፈሳዊ ጦርነት ታጥቀን ልንነሳ ያስፈልጋል። ምድር በኃጢዓት ማጥ ውስጥ እየሰጠመች ነው። በምድር ሁሉ የንጹኃን ዜጎችና ደም በተለያዩ ጦርነቶች እንደ ደም እየፈሰሰ ነው። በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ህጻናት የገቡበት ሳይታወቅ ይጠፋሉ። በቅርቡ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከነዚህ ህጻናት ብዙዎቹ በክፉ ሰዎች ርኩስ ወሲባዊ ጥቅም ይደፈራሉ፣ ይገደላሉ ለአጋንንትም እንደ መስዋዕት ይቀርባሉ። ይህ ደግሞ የሚካሄደው ድሃና ያላደጉ በሚባሉ በአፍሪካ፣ በደቡብ አሜሪካና በእስያ ብቻ ሳይሆን ሰልጥነናል፣ በልጽገናል በሚሉት አገሮችም ነው። እኛ  ክርስቲያኖች እነዚህን እኩይ ተግባራት በያለንበት አገርና ከተማዎች የመዋጋት ኃላፊነት አለብን። የህዝብን ደህንነት ከሚጠብቁ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት ጋር በመልካም ስራ መተባበር ግዴታችን ነው። ከዚህ በላይ ግን የችግሩ መንስኤ መንፈሳዊ ነውና፣ ይህንን ክፋት የሚያቅዱትንና የሚያስፈጽሙትን የጨለማውን ዓለም መንፈሳዊ ኃይላት ከአምላካችን ጋር ወደ ጽድቅ ጦርነት በመግባት መዋጋት አለብን። ታዲያ ወደዚህ ጦርነት ለመግባትና ድል ለማድረግ ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ሰራዊት መቀደስ አለብን። በዘሆልቁ ምእራፍ 10 ላይ ጌታ አምላክ እንዳዘዘው የጦርነትን መለከት የሚነፉት ካህናት ናቸው። ካህናት ደግሞ ለእግዚአብሔር የተቀደሱ፣ የተመረጡ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ጠንቅቀው የሚያውቁና በእግዚአብሔር ሥርዓት የሚሄዱ ሰዎች ናቸው። ወታደር ወደ ጦርነት ሲወጣ ብዙ ኮተታ ኮተት ተሸክሞ አይሄድም። መንፈሱን፣ አእምሮውንና ሰውነቱን ለጦርነት ያዘጋጃል። የመዋጊያ መሳሪያዎቹን ይይዛል። አብረውት የሚዋጉትን ሰዎች በሚገባ ይተዋወቃል። በጦር ሜዳ ላይም የሚግባቡባቸውና ለመረዳዳት የሚያስችሉአቸውን ቋንቋ ይማራሉ። ከአስር አለቃ ጀምሮ እስከ ጀነራል ድረስ መሪዎቻቸውን በሚገባ ያውቃሉ። ሁሉም ጠብመንጃ ይዘው ተኳሽ ብቻም አይደሉም። አንዳንዱ ስንቅ ያዘጋጃል፣ አንዳንዱ ያቀብላል፣ አንዳንዱ የቆሰሉትን ያክማል፣ ሌላው የደከሙትን ያበረታታል ወዘተ። ታዲያ በመንፈሳዊ ጦርነት የምንሳተፍ ክርስቲያኖችም ከዚህ ባላነሰ መዘጋጀትና መሰማራት ያስፈልገናል። ያንተ፣ ያንቺ ድርሻ ምንድ ነው? ያለ ጥርጥር ጌታ የጨለማውን ኃይል በመጋፈጥ የወንጌልን ብርሃን ጌታን ላላወቁት እንድናደርስ አዝዞናል። መለከት ተነፍቷል። አምላካችን በፊታችን ወጥቷል። ከታዘዝን፣ ለሱ ከተገዛንና በጽድቅ ከተዋጋን ድል ማድረጋችን የተረጋገጠ ነው። ንጉሳችንን ተከትለን በምስጋና፣ በዝማሬ፣ በጽድቅ፣ በቅድስና፣ በእውነት፣በትጋት፣ በፍቅር፣ በርህራሬና በትህትና እንውጣ። እንጸልይ። ቃሉን እናንብብና እናጥና። የወደቁትን እናንሳ፤ ተስፋ ያጡትን አይዞአችሁ እንበላቸው፣ የተበተኑትን እንሰብስብ፣ ጌታ ቀብቶ የላከልንን መሪዎች በትክክል እንለይና እንከተላቸው፤ ፍቅራችን በእውነትና በተግባር እንጂ ከንፈርን በመምጠጥና በማስመሰል አይሁን። የመለከቱን ድምጽ እንስማ።

የመለከት ጥሪ ለመንፈሳዊ ጦርነት

የመለከት ጥሪ ለመንፈሳዊ ጦርነት

ባለፈው መልዕክቴ ላይ ባጭሩ እንደጠቀስኩት ከማንኛውም የድምጽ ወይም የሙዚቃ መሳሪያ ይልቅ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መለከት ለብዙ አገልግሎት ሲውል እናየዋለን። ታዲ መለከት ሲነፋ ሁል ጊዜ ትርጉምና መልዕክት አለው። የእግዚአብሔር ሕዝብ ደስ ሲለውና ድል ሲያደርግ ለምስጋናና ለአምልኮ መለከት ይነፋል። በብሉይ ኪዳን ዘመን በኢየሩሳሌም በሚገኘው በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ በየእለቱ መስዋዕት በሚቀርብበት ጊዜ መለከት ይነፋ ነበር። ጌታ አምላክ ራሱ ነው ሙሴ ቢያንስ ሁለት የብር መለከቶችን እንዲሰራ ያዘዘው። መለከት መቼ፣ ለምን እና እንዴት እንደሚነፋም በዝርዝር ትዕዛዝን ለሙሴ የሰጠው ጌታ ራሱ ነበር። ይህም በኦሪት ዘኈልቁ ምእራፍ 10 ከቁጥር 1 እስከ 10 ድረስ ተጽፎልናል። ዛሬ እንድናተኩርበት የምሻው የመለከት አገልግሎት ግን እኛ እንደ እግዚአብሔር ሕዝብ ከኤደን ገነት ጀምሮ በዓለማችን ላይ እየተካሄደ ያለውን መንፈሳዊ ጦርነት እንዳንዘነጋና ነቅተንም እንድንዋጋ ለመቀስቀስ ነው። የመለከት አገልግሎት በብሉይ ኪዳን የቆመ ነገር አይደለም። በደስታና በድል ጊዜአችን በመለከት፣ በበገና፣ በመሰንቆ፣ በከበሮና በሌሎችም መሳሪያዎች ጌታን ማምለካችንና መዘመራችን መልካም ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልሶ እስኪመጣ ድረስ ግን የግድ መንፈሳዊ ጦርነቶች አሉብን። ሓዋርያው ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 14፤8 ላይ ወደጦርነት የሚቀሰቅስ የመለከት ድምጽ እንዳለ አስተምሮአል። በ2ኛ ሳሙኤል 2;28 ላይ ደግሞ ጦርነትን ለማቆምም መለከት እንደሚነፋ እንማራለን። የክርስቲያን ጦርነት በዚህ ዓለም ካሉት ጦርነቶች ሁሉ እጅግ ከባድ፣ የመዋጊያ መሳሪያዎቹም የተለዩ እና መንፈሳዊ መሆነቸውንም ይኽው ሓዋርያ በ 2ኛ ቆሮንቶስ ምዕ 10 ቁጥር 3 እስከ 6 ድረስ ተጽፎልናል። የምንጋደለው በመንፈሳዊ ስፍራ ከሚገኙ፣ ነገር ግን ይህንን እኛ የምንኖርበትን ቁስ አካላዊ ዓለምም ሊበጠብጡ እና የሰውን ዘር ለማጥፋት ከሚዋጉ የጨለማው ዓለም አለቆች፣ ከሥልጣናት፣ ከገዢዎችና የክፋት መንፈሳውያን ሰራዊት ጋር ነው። ኤፌሶን 6፤10 እስከ 20። በዚህ ጦርነት ውስጥ እያንዳንዳችን የመዋጋት ግዴታ አለብን። ያለን ምርጫ ጠላትን መዋጋት ወይም እጅ ሰጥተን የጠላት መጫወቻ መሆን ነው። በጸጋ ድነናልና መዋጋት ምን ያስፈልጋል የሚል ክርስቲያን የወንጌል መልእክት አልገባውም። አዎን በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው በክርስቶስ የዳንነው። ነገር ግን ያው ያዳነን ጌታ ደግሞ በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ብሎናል። መስቀሉንም ተሸክመን እንድንከተለው ጠርቶናል። ከጦርነቶቻችን አንዱ ለምድራችንና ለምንኖርበት አገር እንዲሁም ምድርን ለሚመሩት የታላላቆቹ አገሮች መሪዎች መጸለይ ነው። ሌሎች ክርስቲያን መሪዎች ስለ አገራችን ስለ ኢትዮጵያ እንድንጸልይ አሳስበውን ስንጸልይ ቆይተናል። ዛሬ ደግሞ ስለ ታላላቆቹ የምድር መንግስታት፣ በተለይም ደግሞ ስለ አሜሪክ እንድንጸልይ በጥብቅ አሳስባችኋለሁ። በፊታችን ያለው ጊዜ ምድር እጅግ ወደ ትልቅ አደጋ እየተፋጠነች ያለችበት ወቅት ነው። የአሜሪካ ምርጫ አለፈና አንድ ወገኑ አሸነፈ ቢባልም፣ ከዚሁ ከምርጫው ጋር ከተያያዙ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ አገሪቱ ገና አልወጣችም። ለአሜሪካ እንጸልይ። መቼም የኣሜሪካ ክፉ ነገር ውስጥ መውደቅ ምድርን ሁሉ፣ እኛንም ሁላችንን በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ እንደሚጎዳ የምንክድ አይመስለኝም። በሚቀጥሉት ሳምንታትና ወራት የሚደረገው የስልጣን ሽግግር ሰላማዊ እንዳይሆን የሚቀሰቅሱ ብዙ ጥሪዎችና ጥረቶች መኖራቸውን ሁኔታውን በቅርብ የሚከታተሉ ባለሙያዎችና መሪዎች እያስጠነቀቁ ነው። ለአሜሪካ እንጸልይ።  ባለፉት ጥቂት አመታት ዓለማችን በተፋጠነና በሚያስፈራ ሁኔታ ወደ ጦርነት እየተገፋች ነው። የሮማው ሊቃነ ጳጳስ ፍራንሲስ ደጋግመው ሲናገሩ በምድር ላይ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት በትንሽ በትንሹ ጀምሮአል ብለዋል። እጅግ ታላላቅና አስፈሪ የሆኑ የአሜሪካ፣ የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የቱርክ፣ የሩሲያ፣ የቻይና፣ የኢራን፣ የሰሚንና የደቡብ ኮሪያ የጦር ሃይሎች በሰሜንና በምስራቅ አውሮፓ፣ በጥቁር ባህር፣ በሜዲትራኒያን ባህር፣ በኢራንና አካባቢው በሚገኘው የፋርሱ ባህረ ሰላጤ ፣ በደቡብ የቻይና ባህር፣ በኮሪያ ባህረ ሰላጤ ዙሪያ ሰፍረዋል። ብጥብጥ፣ ጦርነትና እልቂትን ጌታ አምላክ አልፈጠረም ይህም ፈቃዱ አይደለም። አሁን ምድርን የሚያሰጋት ደግሞ እጅግ የሚያስፈራ የኑክሊየር  ጦርነት ነው ። የኑክሊየር ጦርነት ማለት ምን እንደሆነ አብዛኛው የሰው ዘር አያውቅም። ወገኖች ስለዚህ ለመጻፍ አሁን ቦታ አይበቃኝም። ነገር ግን ይህንን የመለከት ጥሪ እንስማ። በገና እና በአዲስ አመት ዋዜማ ለምን ስለዚህ ዓይነት ነገር ትናገራለህ ብትሉኝ ይገባኛል። ገናን እናክብር። አዲስ አመትንም በተስፋ እንቀበል። ነገር ግን የእግዚአብሔር መንፈስ ደግሞ ዘመኑን እንድንለይና በምድር ሁሉ ላይ አንዣቦ ስላለው ጥቁር ደመና እንድንጸልይ ይህንን የመለከት ድምጽ እንዳሰማ ግድ ይለኛል። ለአሜሪካ፣ ለካናዳ፣ ለሌሎቹም ታላላቅ መንግስታትና ለአገራችንም ኢትዮጵያ እንጸልይ። እኛ የክርስቶስ ነን። በህይወትም ሆነ በሞት የምንፈራው ነገር የለም። ነገር ግን ጌታን ላላወቁትና ለዘላለም ሊጠፉ ላሉት ህዝብ ሁሉ እንዲጸልይ ከኛ ይልቅ ጌታ ማንን ይጥራ? የዛሬው የመለከት ድምጽ ይህ ነው።  እንጸልይ !!

ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂ የምድርን አየር እያናጋ ነው፣ የምድር መንቀጥቀጥና እሳተ ገሞራም የማፈንዳት ጥፋቶች ይሰራሉ

በኖኅ ዘመን እንደነበረው የሰው ልጅ እግዚአብሔርን ክዶ ራሱ አምላክ ለመሆን ሲቃጣው በራሱ እና በእግዚአብሔር ፍጥረት ላይ ትልቅ ጥፋትን እየፈጠረ ነው። ዶ/ር በፈቃዱ አድማሱ ጌታ አምላክ የሰው ልጅ ሊ...